Reyot Kin: ድምጻዊ አበበ ተካ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬን እንዲህ ይተዝታል፡፡

Sdílet
Vložit
  • čas přidán 20. 03. 2017
  • ድምጻዊ አበበ ተካ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬን እንዲህ ይተዝታል፡፡
    ሙሉጌታ ተስፋዬ ወልድያ ሙጋድ በሚባል አካባቢ በ1946 የተወለደ፣ የተባ ብእር፣ የተዋበ ቋንቋ፣ የጠለቀ ሀሳብ ባለቤት የነበረ ገጣሚና ባለቅኔ ነበር፡፡ በህይወት በኖረባቸው 50 አመታት እጅግ በርካታ ውብና ጠሊቅ ግጥሞችን ጽፏል፡፡ እውነት ከመንበርህ የለህማ፣ ምነው አንተ ሙሽር፣ ደስ ይላል መስከረም፣ የባለቅኔው ምህላ፣ ስምአኒ ከጌቴሰማኒ፣ ወደሚቀጥለው፣ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት፣ ከሰው መርጦ ለሹመትና ሌሎች የበዙ ግጥሞቹ በስነጽሁፍ አፍቃርያን ዘንድ ልዩና ትልቅ ስፍራ አላቸው፡፡ግጥሞቹ በቅርቡ በስንዱ አበበ ሰብሳቢነት የባለቅኔው ምህላ በሚል ርእስ ለገበያ ቀርበዋል፡፡
    ሙሉጌታ ተስፋዬ እጅግ የተወደዱ የዘፈን ግጥሞችን ለተለያዩ ድምጻውያን ሰጥቶ ተጫውተውለታል፡፡ አበበ ተካ፣ ብጽአት ስዩም፣ አህመድ ለጋስ፣ ታምራት ደስታ፣ ዣንስዩም ሄኖክ፣ ሀና ሸንቁጤ፣ ጸደንያ ገብረማርቆስ ግጥሞቹን ካቀነቀኑ ድምጻውያን መሀል ይጠቀሳሉ፡፡ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ ወፍዬ ለተሰኘችው በአበበ ተካ ለተዘፈነች ግጥሙ ከሁሉ የተለየ ግምትና ፍቅር እንዳለውም ገልጽዋል፡፡ “ወፍዬን” ይላል ሙሉጌታ፡፡ “ወፍዬን፣ አማርኛ ቋንቋ በህይወት እስካለ ድረስ፣ አማርኛ የሚችል ሰው በህይወት ዘመኑ ሁለቴ ባይሰማት፣ ቢያንስ አንዴ ሊሰማት ግድ አለበት”
    ሙሉጌታ ተስፋዬ ምንም እንኳ ለቁጥር የበዙ ድንቅ የጥበብ ውጤቶችን ቢቸረንም፣ ብርሃኑን ሳንመለከትለት፣ እውነቱን ሳናጎላለት፣ እሳቱን ሳንሞቅለት፣ ህመሙን ሳንጋራለት፣ እንደሚገባ ሳናከብረው ያለፈም ባለቅኔ ነው፡፡
    ድምጻዊ አበበ ተካ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬን እንዲህ ይተዝታል፡፡
  • Zábava

Komentáře • 6

  • @sfhhhffggg6583
    @sfhhhffggg6583 Před 5 lety +6

    የባለ ቅኔው ሙልጌታ ተስፋየ ስራውች አድናዲ ነኝ

  • @arsemahadushe4225
    @arsemahadushe4225 Před rokem +2

    ልጆቹስ

  • @MohammedAhmed-mj6ug
    @MohammedAhmed-mj6ug Před 5 lety +7

    የተገለጠለት ሰው ነበረ😢

  • @sshalom395
    @sshalom395 Před 3 měsíci

    Aye Thewodros thegay😢😢😢 betezeta ye zary 7 ameten asetaweseku 😢😢 senet negere telewete ?💔💔 abeys edet hono yehon ? 😞😞😞

  • @afarawkis
    @afarawkis Před 7 měsíci

    ከሱ የዝረፉትን ግጥሞች መታከሚያ ይሆናችዋል አንዳለው ይሄው መታክም ይዘውበታል ሆዳሞች ዛሬ በስራችሁት ስራ አፍራችሁ አንግታቺሁን ደፍታችሁ ትኖራላቺሁ ትንሽ አንኩዋን ለ ልጆቹን አታስቡም ሆዳሞች

  • @Rose-xh6bk
    @Rose-xh6bk Před měsícem

    ብታምኑኚም ባታምኑኚም አበበ ተካ ሁለት ሶስት ኢንተርቪው ሲያደርግ ሰምቸዋለሁ አንጀቴን ይበላኛል አላቅም ወሬው በሀዘን የተሞላ ነው