Reyot Kin: ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ ሲተዘት፡፡ በቴዎድሮስ ጸጋዬ፡፡
Vložit
- čas přidán 21. 08. 2024
- ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ ሲተዘት፡፡ በቴዎድሮስ ጸጋዬ፡፡
ቀንን ካልወጡት ጤዛ እየላሱ፣
ማጣት ስለት ነው ጥንድ ምላሱ፡፡
ሙሉጌታ ተስፋዬ ወልድያ ሙጋድ በሚባል አካባቢ በ1946 የተወለደ፣ የተባ ብእር፣ የተዋበ ቋንቋ፣ የጠለቀ ሀሳብ ባለቤት የነበረ ገጣሚና ባለቅኔ ነበር፡፡ በህይወት በኖረባቸው 50 አመታት እጅግ በርካታ ውብና ጠሊቅ ግጥሞችን ጽፏል፡፡ እውነት ከመንበርህ የለህማ፣ ምነው አንተ ሙሽር፣ ደስ ይላል መስከረም፣ የባለቅኔው ምህላ፣ ስምአኒ ከጌቴሰማኒ፣ ወደሚቀጥለው፣ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት፣ ዳብሬ ምንህ ክፉ፣ የሰከነች ሰፊና፣ ከሰው መርጦ ለሹመትና ሌሎች የበዙ ግጥሞቹ በስነጽሁፍ አፍቃርያን ዘንድ ልዩና ትልቅ ስፍራ አላቸው፡፡ግጥሞቹ በቅርቡ በስንዱ አበበ አሰባሳቢነት የባለቅኔው ምህላ በሚል ርእስ ለገበያ ቀርበዋል፡፡
ሙሉጌታ ተስፋዬ እጅግ የተወደዱ የዘፈን ግጥሞችን ለተለያዩ ድምጻውያን ሰጥቶ ተጫውተውለታል፡፡ አበበ ተካ፣ ብጽአት ስዩም፣ አህመድ ለጋስ፣ ታምራት ደስታ፣ ዣንስዩም ሄኖክ፣ ሀና ሸንቁጤ፣ ጸደንያ ገብረማርቆስ ግጥሞቹን ካቀነቀኑ ድምጻውያን መሀል ይጠቀሳሉ፡፡ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ ወፍዬ ለተሰኘችው በአበበ ተካ ለተዘፈነች ግጥሙ ከሁሉ የተለየ ግምትና ፍቅር እንዳለውም ገልጽዋል፡፡ “ወፍዬን” ይላል ሙሉጌታ፡፡ “ወፍዬን፣ አማርኛ ቋንቋ በህይወት እስካለ ድረስ፣ አማርኛ የሚችል ሰው በህይወት ዘመኑ ሁለቴ ባይሰማት፣ ቢያንስ አንዴ ሊሰማት ግድ አለበት”
ሙሉጌታ ተስፋዬ ምንም እንኳ ለቁጥር የበዙ ድንቅ የጥበብ ውጤቶችን ቢቸረንም፣ ብርሃኑን ሳንመለከትለት፣ እውነቱን ሳናጎላለት፣ እሳቱን ሳንሞቅለት፣ ህመሙን ሳንጋራለት፣ እንደሚገባ ሳናከብረው ያለፈም ባለቅኔ ነው፡፡
ቴዎድሮስ ጸጋዬ ገጣሚና ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬን እንዲህ ይተዝታል፡፡
ቴዲ አንተ ራስህ የቋንቋ ሀብታም ነህ አያ ሙሌ ደግሞ የግጥም ልዑል 🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Thanks for presenting such great legend
እውነት ነው ግዜ ኣለን ሙሌን ለማወደስም ለማንገሲም
ቴዲ ፈጣሪ ኣብዝቶ ይባርክህ እድሜህን ያርዝመው
ካገርቤት ጀምሮ እስከዛሬ እየተከተልኩህ ነው ኣብዝቼ ኣትርፌ ተዝናንቻልሁ
እናመሰግናለን ቴዲ እጅግ ውብ አቀራረብ ነው።
እዚሁ አልበም ላይ ወፍየ የሚል ሙዚቃ አለ እና የወፍየን ግጥም የሰራው ሙልጌታ ተስፍየ በይበልጥ ብቃቱን ያሳየበት ነው።
Thanks
ሙሌ 1ኛ ነው ማንም አይበልጠውም
Thanks Teddy
"የእብድ ቀን አመሽም "ይል ነበር ሙሉጌታ ይገርማል!!!
Teddy selam lante yihun
Betam des yilale
Be ewent hule yemetakerbew neger hulu des yilale betam new yemeketatelh
Progerameh hule astemari new
Betam enamesegenalen
Ethiopiaya ende ante ayinet sew yibezalat
Tebarek selam lante!!
ይገርማል.በውነት..እናመሠግናለን
Balkene Aya mule nebshen yemarathe🙏
ከ❤እናመሰግናለን ❤🙏
ቴዶ ሰላምክ ብዝት ይበል።
የሙልጌታ ተስፋዬ ሴት ልጅ የቅርብ ጓደኛዬ ነበረች በጣም በአስቸጋሪ ችግር ውስጥ ነበረች ስለ አባቶ አውርታ አትጠግብም ነበር የምትገርመኝ ሞቶም ተስፋ ታረገው ነበር።
ደስ አለኝ በጣም!!
ቴዲ በጣም እናመሰግናለን የውሸት ኖረን የእውነት ለምንሞተው ትልቅ መልክ ያለው ዘፈን ነው
ነብስ.ይማር
Betam yigermal…Taddy eytak gelsak betam diss yilale betam yemigermewu getmune getamiwune eske ahune alwukem neber mulgata tesfaynem nefes yimar ..kechalek abeben tekam betyikelen diss yilgnale
yeleba sewu
ቴዲ የጋዜጠኞች ቁንጮ
Be mesthaf serawochu yigegnalu??
የባለቅኔው ምኅላ የተሰኘ የግጥሞቹ ስብስብ መጽሐፍ አለው
ሙሉጌታ ተስፋዬ የኢሕአዴግ ታጋይ መሆኑን ስንቶቻቹ ታውቃላችሁ?
my best it is false information.i have detail ividence about mulugeta tesfaye.
the new generation does not knew mulugeta tesfaye ,he was died in1996 e.c.that is the reason why we donot know about he.
@biniyam..ጫፍ ይዛችሁ አታውሩ ሲጀመር ቢሆንስ ? የተወጋው ስለ ጥበብ ችሎታው ነው ካልከውጋ አይገናኝም ሲቀጥል ቢሆንስ ችሎታውን ቀነሰው አጠፋው ? አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ጋዜጣ ላይ አምደኛ ሁኔ ይጽፍ ነበር በሗላ እንደውም ፖለቲካውን መነካካት ለህይወቱ እንዳሰጋውና ነጻነት ስላልተሰማው ስራውን እንደለቀቀ ተነግሯል❤
@@habeshapolitics1313 መልስህ መሆን የሚገባው አዎ አውቃለሁ ወይም አላውቅም ነው። ምነው ትርፍ ጫንክ
@@biniamGere6502 ሰው ያልሆነውን ነው እያልክ ስትናገር ዝም እንድትባል ነው? እንዳንተ በአሉሽና በገደምዳሜ የስንት ቅን ሰዎች ስም በሃሰት ጥላሸት ተቀብቶ ቀርቷል ? ባለቅኔው የሚጽፍበት ጋዜጣ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሲባል አምዱ ደግሞ "ባህል" የሚል ነበር በግድ ጎትተህ ፖለቲካ አታስመስል ቢሆንም ደግሞ ሃጢያት አይደለም።