ኢየሱስ ከኀጢአት ስለ ማዳኑ (የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል 16)

Sdílet
Vložit
  • čas přidán 31. 07. 2024
  • ኢየሱስ በምድር ሳለ አምላክነቱን ጥሎ ሰው ብቻ ከነበረ፣ የዓለምን ሁሉ ኀጢአት ሊሸከም አይችልም፤ እናም እስከ አሁን ከነኀጢአታችን በቀረን ነበር። ለድነት አምላክ አምላክነቱን ሳይተው ሰው መሆኑ ግድ ነው። ምክንያቱም አምላክ ሰው ባይሆን ኖሮ መሰቀል አይችልም፤ አምላክ ረቂቅ ነውና! ሰው ብቻ ቢሰቀል ደግሞ ዓለምን ሊያድን ባልቻለ ነበር። ኢየሱስ ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ የኀጢአት ዕዳችንንም የሚከፍለው እንደ ሰው ብቻ በሆነ ነበር። የኀጢአት ዕዳ ዘላለማዊ ነው፤ በውሱኑ ሰው ተከፍሎ አይጨረስም። በመሆኑም ማንም ዕዳውን ማወራረድ አይችልም፤ ለዘላለም ሲከፍል ይኖራታል እንጂ። ኢየሱስ ኀጢአት የሌለበት ሰው ሆኖ እንኳ ይህን ማድረግ አይችልም። ስርየት ተግባራዊ የሚሆነውና ተፈጻሚነት የሚኖረው ጌታ ኢየሱስ ከሰዎች ወገን ምሉእ ሰው፣ ከአምላክ ወገንም ሙሉ አምላክ የሆነ እውነተኛ መካከለኛ ከሆነ ብቻ ነው። የኢየሱስ ሰው-ነት ከተጓደለ፣ ስርየት የተጓደለ ይሆናል፤ የኢየሱስ መለኮትነት ከተጓደለም ስርየት የተጓደለ ይሆናል። ስርየት ከተጓደለ ደግሞ ከነኀጢአታችን እንቀራለን። ኢየሱስ በሰው-ነቱም ሆነ በመለኮትነቱ ምሉእ ከሆነ ግን፣ የእርሱ ሞት አምላክ በራሱ ሰው-ነት የፈጸመው ሥራ እንጂ የሰው ብቻ ድርጊት አይሆንም።

Komentáře • 11

  • @Kidist_
    @Kidist_ Před rokem

    Thank you, Paulos! Many blessings 🙏

  • @selamsemanhe-iw3jy
    @selamsemanhe-iw3jy Před rokem

    እግዚአብሔር የባህሪያቱ ድምር አይደለም 🙏❤🙏
    የኢዮብ ቅሬታ በክርስቶስ ተመልሶል
    እግዚአብሔር ሰው ሆኖ መካከለኛ ሆኖልናል
    ሃሌሉያ
    ግን ይሔ የአዲስ ኪዳንን ሰዎች ብቻ የሚመለከት አይደለም የእግዚአብሔር ሰው መሆን ወደ ኃላም የሚመለከት ነው ምክንያቱም በብሉይም የኃጥያት ስርየት አልነበርም እንደውም መስዊያወቹ ኃጢያትን ያስታውሱ ነበር
    #ቀድሞ የተፈፀመውን ኃጢያት ሳይቀጣ በማለፍ
    ኃጢያት የሚቀጣበት ቀን አለ በማለት በይደር አቆይቶት ።
    #መስቀሉ የእግዚአብሔር ፍቅርም ቅድስናም መገለጫ ነው 🙏❤🙏
    የብሉይ ሰዎች መስቀሉን ወደፌት በማየት ሲደኑ
    የአዲስ ሰዎች መስቀሉን ወደኃላ በማየት ይድናሉ
    #አንድ መዳኛ አንድ አዳኝ 🙏❤🙏
    እግዚአብሔር ይስጥል

    • @PaulosFekadu
      @PaulosFekadu  Před rokem +1

      ተባረኪልኝ።

    • @selamsemanhe-iw3jy
      @selamsemanhe-iw3jy Před rokem

      @@PaulosFekadu አሜን በአንተ የተማረኩበት ቀን ይባረክ ጨካኝ አርጓኛል ብዙ ፍቅር ብዙ ክብር 🙏❤❤🙏

    • @abebeabdissa1524
      @abebeabdissa1524 Před 8 měsíci

      በጾም በጸሎት ሆኜ በዚህ ድንቅ ትምህርት ተጠቀጠቅኩ!

  • @mancity5551
    @mancity5551 Před rokem

    መዳኛው አንድ ብቻ ከሆነ በብሉይ ዘመን የነበሩ አህዛብ በምን ሊድኑ ነው?ህግን ሳያውቁ ነብያት ሳይላኩላቸው ስለሚመጣው መሢህ ሳይሰሙ እንዴት ሊፈረድባቸው ነው, ወንጌል ያልሰሙ ስለኢየሱስ ሰምተው ቢሆን ኖሮ የማመን እድል ሊኖራቸው ነበር እኮ

    • @selamsemanhe-iw3jy
      @selamsemanhe-iw3jy Před rokem

      እባክዎ ከክፍል አንድ ጀምረው ይማሩ 🙏

  • @mancity5551
    @mancity5551 Před rokem

    የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው መቼ ነው? ከማርያም ሲወለድ ወይስ ከመጀመርያውኑ?
    ኢየሱስ ከአብ የወጣ ከሆነ, መንፈስ ቅዱስስ ከአብ ስለሚወጣ ለምን የእግዚአብሔር ልጅ አልተባለም?

    • @selamsemanhe-iw3jy
      @selamsemanhe-iw3jy Před rokem

      ከክፍል 1 ጀምረው ይማሩ 🙏

    • @PaulosFekadu
      @PaulosFekadu  Před rokem

      ከክፍል 1 ጀምሮ ትምህርቱን መከታተል ለዚህ ጥያቄ መልስ ያስገኛል። እባክዎን ይሞክሩት