ማደሪያውን መውደድ መዝሙር 84
Vložit
- čas přidán 22. 06. 2021
- በዘመናችን አይተነው ከማናውቀው ዓለማችንን ከወረረ ብዙዎችን በደዌ ካደቀቀና ሚሊዮኖችን በሞት ከነጠቀ ወረርሽኝ ውስጥ እየወጣን ነው። በዚህ ጊዜ በአካል ተሰብስቦ ማምለክ ስላልተቻለ አቅሙ ያላቸው በቴክኖሎጂ ታግዘው በርቀት ያልቻሉም በቤታቸው ተቀምጠው ከርመዋል። አሁን ግን እንደ ቀድሞው በአካል ተሰባስበን የምናመልክበት በር እየተከፈተ ነው። መሸሸግ ባለብን ጊዜ መሸሸጋችን መልካም ሲሆን በአካል መሰብሰብ ባለብን ጊዜ መሰብሰቡ ለነገ የማይባል ጉዳይ ነው። በእርግጥ ባደጉት አገራት ለምንኖር በዙም እና በስልክ የምናደርገው ሕብረት ከፍተኛ ምቾት ስላለው ወደ በፊቱ ለመመለስ ጊዜ ሳይወስድብን አይቀርም። ሆኖም የቅዱሳንን በአካል ተገናኝቶ ጸጋ መካፈልን ሊተካ የሚችል ምንም ነገር የለም። ከዚህ በመነሳት ቀደም ሲል በእግዚአብሔር ቃል "ሕዝቤ ሆይ ና! ወደ ቤትህ ግባ! ቁጣ እስኪያልፍ ድረስ ለጥቂት ጊዜ ተሸሸግ" ሲለን የነበረው ወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁን አሁን ደግሞ "ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው!" በማለት ወደ አካላዊ ሕብረት እንድንመለስ ይመክረናል። ይህ መዝሙር (መዝ. 84) ከመዝሙሮች ሁሉ እጅጉን የተወደደና በአንድ የእግዚአብሔርን ቤት አደባባዮች በናፈቀ፣ ከቆሬ ልጆች መሐል የሆነ ሌዋዊ በፍቅር፣ በናፍቆት፣ በቅዱስ ቅናት እና በእርካታ የዘመረው ነው። ዛሬ የእግዚአብሔር ማደሪያ በኢየሩሳሌም የሚገኝ መቅደስ ሳይሆን በአቅራቢያችን ያለ የቅዱሳን ሕብረት ነው። ይህም በኢየሩሳሌም ነጭ ድንጋዮች ሳይሆን ከክርስቶስ በተገኘን ሕያዋን ድንጋዬች ተገጣጥሞ የተሠራ ነው። ስለዚህ ብርድ ልብሳችንን ገፈን፣ ከአልጋችን ተስፈንጥረን ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ፤ ማደሪያዎቹን (ቅዱሳንን) እንውደድ፣ አብረናቸውም እናምልክ። መልካም የመልዕክት ጊዜ።
አሜን ማደረያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸዉ ተባረክ ጸጋና እደሜ ይጨምረልን
Yaredo anten yeseten Egziabiher ybarek.
ይገርማል መምህር የንተን ትምርት የዮሐንስ ወንጌል ብቻ ቀርቶኝ እሱን እየተከታተልኩ ይሄ ትምርት ሲለቀቅ ደስ አለኝ እያለቀብኝ እየደጋገምኩነው የምሰማው ትምርቶችህን በተለይ ዮሴፋ የፋሬዛፋ 10ግዜ ይሆናል የደጋገምኩት እጅግ እድሜ ከጤና ይስጥህ እኔ ኦርቶዶክስ ነኝ የጌታን ቃል ግን እንደ ቆየ ወይን ጠጅ እየጣፈጠኝ እንድታነፅበት አርገሀኸኛል
ወንድም ሚካኤል, በጣም ጥሩ ነው የእግዚአብሔርን ቃል መስማትህ አንድ ነገር ታውቃለህ ብዬ አምናለሁ መዳን በክርስቶስ ብቻ እንደሆነና ልንድንበት የተሰጠን ስም ከሰማይ በታች ኢየሱስ ብቻ እንደሆነ እንድታውቅ እፀልይልሃለሁ:: ጌታ ይባርክህ!!
እጅግ የከበረ፣የእውነት መርሕን የተከተለ፣ ወቅታዊ መልዕክት፣ሁልጊዜ ልናስበው፣ልንጠብቀውና የሕየወወታችን መመሪያ አድርገን ዘወትር በሐሳባችን ፊት ለፊት ላይ ከፍ አድርገን ልናቆመው የተገባ ትምሕርት ነው፣፣
ያሬዴ፣
በረጅም እድሜ ከነሙሉ ጤንነትሕ ተባረክ።
እውነት ነው ተባረክ ወደ እግዚአቢሄር እንሄድ ሲሉኝ ደስ አለኝ ነው ዩሚሎው አሜን ይዝራብን
የእግዚአብሔር ሰው ያሬድ የምታስተላልፈው ትምህርት እጅግ በጣም ድንቅ ነዉ ዘመንህ ይባረክ እንደዉ በጌታ ፍቅር አንድ ጥያቄ እጠይቃለሁ በትምህርት ይልቀቅ አንድ አንድ ሰዎች ክርስቶስ ከአዳም ዘር ተካፍለዋል ይላሉ ለሎቹ ከማርያም ደምና ስጋን ተካፍለዋል ይላሉ ዕብራውያን 2/14/15 በጥቅስ በጌታ የሆኑት ናቸው ስለዝህ ጉዳይ በጥልቀት ቢታስተምር ደስ ይለኛል
God bless You dear brother Evangelist Yared Tilahun!!!
ሃሌሉያ የመቅደስ ሽግግር አደረጉ ያኛውን መቅደስ ትተተው ምን መጣ ብለው ወደዚኛው መጡ ሕዝቡን
በፉጨት ጠራ በሺህ የሚቆጠሩ ይህ ድምጽ ምንድ
ነው ብለው መጡ ስትል እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ዕብራዊያን 1-3 በልጁ በዚህ ዘመን
መጨረቫ ለኛ ተናገረን እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና
የባህርው ምሳሌ ሆኖ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ
ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኃላ በሰማያት በግርማው ተቀመጠ
ክብር ሁሉ ለኢየሱስ ይሁን
የማከብርህ ወንድሜ ወንጌላዊ ያሬድ ላንተና ለቤቴሰቦችህ ሁሉ አሁንም የላይኛው ምንጭ
የታችኛው ምንጭ ይፍለቅላችሁ ተባረክ
እግዚአብሔር ይባርክህ ፀጋው ይብዛልህ ወንጌላዊ ያሬድ
አንተ ስታስተምር ነገሮች ግልጥልጥ ነው የሚልልኝ። ጌታ ይባርክህ ፓስተር ያሬድ።
The unseen God . . . I can see you in your doweling place Amen 🙏🏼
ወንድም ያሬድ እግዚአብሔር ይባርክህ:: በትምህርቶችህ በጣም ተጠቅሜአለሁ እግዚአብሔር ይህንን ፀጋ ስለሰጠህ ስሙ ይባረክ::
አወነተኛ የወንጌ አስተማሪ..... ተባረክ
ጌታ አብዝቶ አብዝቶ ይባርክህ
ወንድሜችን ያሬድ ጌታ ይባርክህ ዘመን ሁሉ ከነ ቤተሰብህ በጌታ ቤት ይለቅ
ጌታ ይባርክ እናመሰግናለን
ባዲስ ኪዳን ማደሪያቹ እኛበ ክርስቶስ እንደገና የተወለድን ክርስቲያኖች ነን የሥላሴ ማድሪያዎች ነን
እግዚአብሔር ተናገረ እኔም ሰማሁ! ወንድሜ ያሬዶ ጌታ ይባርክህ!
እግዚአብሔር ይባረክ❤
ያሬዱ የስማሁት ገና ስትለቀው ነው ስሞኑን ውስጤ ሳስበው ነበር ይህን ትምህርት አሁንም ውስጤ ላይ አለ እግዚአብሔር ይባርክህ
እጅግ የተወደድክ የእግዚአብሔር ሰው ያሬዶዬ ጌታ ሕይወት ዘመን ዘላለምህን ይባረክ 🙏🙏👏👏👏ድንቅ ትምህርት ነው 👏👏👏👏👏👏❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የምወድህ የአባቴ ልጅ ተባረክልኝ
God bless Brother Yaredo
God bless you wengelawi yared
Yemedeqe temhret new bezu temerebetalehu. Tebark yechemerleh
እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ። ተባረክ 🙏🏽
ወንድም ያሬድ የጌታ ፀጋ እየበዛ ይብዛልህ 🙏🙏🙏
እግዚአብሔር ይባርክህ። የሙሽራይቱን ፍቅር ይመልስልን። እነ ኤርምያስ ስለ ራሳቸው ሳይሆን ስለ ጽዮን ነበር ጩኸታቸው።
Geta ybarek sleant ageliglot
God bless you W/l yared 🙏🙏🙏
Thanks God
ታላቅ ወንድማችን የእግዚኣብሄር ሰው ወንጌላዊ ያሬድ አሁን ካለህበት መንፈሳዊነት ብዕጥፍ ድርብ ጨምርልን ባስተማርከው ትምህርቲ ኣምላካችንን እንድንናፍቅ እንዲሁም የቅዱሳኑን ህብረት ዋጋ እንድንሰጠው ስላደረከን ይሄ የሰበከን አምላክ ይባርክህ ካንተ ብዙ ተምርያለው ባስተማርክ ቁጥርም እንደምማር አምናለው እንደገና ሳንዲያጎ ብትመጣም ጥሩ ነበር። ስላንተ እግዚኣብሔር የተባረከ ይሁን ።
እግዚአብሔር ይባርክህ ወንድሜ አስደነቅ መልዕክት ከትክክለኛ ምንጭ የሚፈልቅ በረከት
እንኳን በሰላም በጤና መጣክል ወንጌላዊ ያሬድ
Yaredo zemeneh agalgiloteh yibarek be ante lay silalewu yekeberewu liyu ye tsega setota getan amesegenslehu andebetocheh yibareku ahunem kezih bebeleta tsega yigenagneh ewnet newu yihe melkekt le ene new 1amet ke hibret teleyiche neber.
Amen
Makon mareke...stotanim le beta chrstian seta....anten marko le egna ye seta Gata ybarek!!!!!!!!!!
አሜን! !አሜን!!አሜን!!አሜን!! ጌታ ሆይ እርዳን ! የተወደድክ ወድማችን ያሬዳችን ስለ አንቴ እግዚአብሔር አሚላክ ይባረክ !!🙏🙏💕💜እንወድሃለን 💙💕
አሜን ህያዋን ማደሪያ ያደራጋን ጌታ ይመስጌን አንቴንም ጌታ ይባርክ በብዙ
Amen 🙏amen 🙏 God bless you and nice to see you again
ወንድሜ ያሬድ ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርክህ !!! በጣም ድንቅ እና እውነተኛ መልእክት ነው። በዚህ ዘመን ከእኛ ህይወት እየደበዘዘ የመጣ ግልፅ የሆነ ት/ት ነው። ጌታ መንፈስ ቅዱስ በአንተ በኩል ግልጹን ስለነገረኝ አመሰግነዋለሁ አንተም ተባረክልኝ !!!
ያሬዳ bro ጌታ እየሱስ ይባርክክ በየሳምንቱ የምታሰተምረው ትምርት እንዴት እንደምባረክ አባክክ አትጥፉ
ይህን ትምህርት ሌላ ቃል ባገኝለት እኔም ዋው ዋው ዋል እንዲሁ ልበል
God Bless you
እልልልልልልልልል 🙏
እጅግ የከበረ፣የእውነት መርሕን የተከተለ፣ ወቅታዊ መልዕክት፣ሁልጊዜ ልናስበው፣ልንጠብቀውና የሕየወወታችን መመሪያ አድርገን ዘወትር በሐሳባችን ፊት ለፊት ላይ ከፍ አድርገን ልናቆመው የተገባ ትምሕርት ነው፣፣
ያሬዴ፣
በረጅም እድሜ ከነሙሉ ጤንነትሕ ተባረክ።
ግሩም! ድንቅ፣ ክብር ያለው መልዕክት ነው! የጌታ ፀጋ ተትረፍርፎ ይብዛልህ ያሬድዬ! እወድሃለሁ!
አሜን አሜን አሜን 🙏🙏🙏🙏
ኣዎን እንኳን ደህና መጣ።
ይባረክ።
ተባረክልን ውድ ያሬዳ።
Yemwedih silagegnewuh betam dess blognal
"Yemekdes shigigir " Egziabiher ymesgen.
I was searching everday ...wellcome back dear teacher yared
Me too every day searching if anything new. I'm glad too welcome brother yared
Blessed😍
ጌታ አብዝቶ አንተንም ቤተሰብህን ይባርክ🙏🏽💕
GOD bless you yaredo❤
Welcome back yarddo God bless you 🙏
Amen hallelujah 🙏🏼
I can literally listen 👂 to you every day .. Powerful teaching .. can you teach about Fasting pls if you can or if you already have can u leave a link here pls ? Much appreciated and I thank God fir saying YES to your calling .. Thank you God bless you ..
Bless you Yared!I am really blessed from your teachings!
Welcome back we miss u.hope u had good time to pray
Waaw great messege thanks evangelist Yaredoo.
Yeredo tefache dese belogale
Tebareke wedeme geta ne benete selemaye dese yelegale 🙌🙌
Amen 🙏🙌, wondme Yared geta Eyesus babizu yebarki yasfeh
Amennnnnn Haleluya Ellllll thanks god
Yarediye it is a great teaching God bless you more!!! Miss you all!!!
HOOOO በየሱስ ስም አይኔን ማመን ነው ያቃተኝ ውድ የኔ ወንድም የሬዲ .......endelig du tilbake……godt å se deg igjen 🙏🏽😇😇
Amen!!!!!!!!!!!!!!!!
Y a r e d a c h i n e e e e.......much respect
God bless you brother Yared.
Amazing the word of God. God bless you!
AMEN.be blessed
ያሪዬ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ!!!
WOW, I'M TOUCHED, WITH THE GOSPEL OF GOD, GBU GLORY TO GOD!!!
God bless you
በሰላም ነው የጠፉህው ያሬድ ?
tebarek mor
GOD bless you more than ever before evangelist yared
እግዚአብሔር ይባርክህ። የሚገርም መረዳት ነው። እኔ ብዙ ጊዜ አንብቤዋለሁ በተለያዮም ሰባኪዎች ሰምቻለሁ እኔ እንደተረዳሁት ነበር ስሰማ የኖርኩት። በተለይ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው። የሚለው ቃል አዲስ መረዳትነው እግዚአብሔር መገለጡን ያብዛልህ ተባረክልን🙏❤
Geta zemnknen yebark!
ያሬዶ እንኩዋን ደህና መጣህልን
ሻሎም ያሬዶ
ሰላም ያሬዶ
እባክህ ወንድም ያሬድ ገላትያ መፅሀፍን አስተምረን
ሰላምህ ይብዛ ጋሽ ያሬድ ጠፋህብን
ሃሌ ሉያ ያሬዶ አንተ ስታስተምር ማስተዋል እችላለሁ ። አንተ ጥቅስ ጠቅሰህ ሳትጨርስ እኔ እጨርሰዋለሁ።
ጠፍተህብን ናፍቀህን ነበር
የ
2ይ ዜና መዋእል 2
11፤ ሑራም ንጉስ ጢሮስ ድማ ደብዳበ ጽሒፉ፡ ንሰሎሞን ከምዚ ኢሉ ምላሽ ሰደደሉ፡ እግዚኣብሄር ንህዝቡ ስለ ዝፈተዎ፡ ንኣኻ ኣብ ልዕሊኦም ንጉስ ገበረካ።
Thank you. To have wonderful teacher lead by Holy Spirit like you Evangelist Yared stay blessed with your family 🙌🏽
እኔ ግን
ቤ/ክ መሄድ እፈልጋልሁ ግን one way 2hr መንገድ ነው
ይሁና
የቆሬ ልጆች እንማን ናቸው?
14 መዝሙሩች የቆሬ ልጆች መዝሙር ነው።
ቆሬ የሊዊ ልጅ ነው የኮራት ልጅ ነው አራተኛ ትውልድ ነው ። አንድ ጊዜ ትልቅ ነውጥ በእስራኤል ዘንድ ተደርጎ ነበር በነሙሴ ላይ ቆሬ እዛ ላይ የነበረ ሰው ነው። ዘኸልቁ 26፥ 16 ይሄ የአመፅ ታሪክ ተወስቷአል። የቆሬ ልጆች መሞት ቢኖርባቸውም ለይቶ ግን የቆሬ ልጆች አልሞቱም በምህረት የተረፉ ናቸው። ለእግ/ር ምህረት ልዩ መረዳት አላቸው። በዳዊት ዘመነ መንግስት የመዘምራን አለቆች አደረጋቸው።
እንግዲህ ከቆሬ ልጆች አንዱ በየበአላቱ ይሄ ሰው ረጅም የእግ/ር ቤት ልምምድ አለው፤ ይሄን መዝሙር ሲዘምር ግን መገኘት አልቻለም።
ከፅሁፍ የእግ/ር ቤት እንዴት እንደሚወደድ ያሳያል። "
የሰራዊት አምላክ ማደሪያዋችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው" የሠራዊት ጌታ የሚያመለክተው የሰማይ አካለትን መላዕክትን ነው። ይሄ እግ/ር በእልፍ መላዕክት የሚታጀብ ነው፤ ነገር ግን ይሄ ጌታ ሕዝቡ ዘንድ ማደር ወደደ። መቅደስህን አይቶ በፍቅር አለመውደቅ አይችልም። "ነፍሴ አደባባዮችህን ትወድዳለች፣ትናፍቃለች” my soul longs, faints እስካደርግ ድረስ ለብዙ ነገሮች ሰዋች faint ያደርጋሉ። ልብ በሉ የድንኳኑ ማማር ላይ አይደለም፣ይልቁንስ አንተ ስላደርክበት ውብ ነው። ምን ማለት ነው ማደሪያዋችህ፦ አንተ ማትታይ አምላክ ነህ፤ በማደሪያህ ግን አንተን አይሃለሁ። አንተ ማትታይ አምላክ ነህ ያየሁህ በዚህ ማደሪያ ነው። አደባባዮች የተባለበት ውጫዊ የሆነው የድንኳን አካል ነው እንደዚህ ያደረገው። 12 ነገዶች በዚህ አደባባይ ይኖራሉ ፣ስንት ውድ ሰው እዚያ ያያል፤ ስጦታቸውን ይዘው ይመጣሉ፤ የሚገርም አይነት felowship
መናፈቁን በሶስት አካላት በመቅናትያስቀምጣል።
① ቁ³ ቀናሁ ትር በሚሉት ወፎች፤ እነርሱ እንኳን ይገባሉ ጫጩታቸውን ይፈለፍላሉ ፤እነዚያ ወፎች ምንኛ የታደሉ ናቸው። ሰው ቢቀና ቢቀና በወፍ ይቀናል? ወፎች መኖራቸውን እንኳን አንገነዘብም
②በማደሪያው በሚያገለግሉት ካህናት ‘ በቤትህ የሚኖሩ’ ‘ የተመሰገኑ አመስገኞች’ የተባረኩ ናቸው። ዕድለኞች ናቸው የተመረጡ ናቸው።
③ ወደ ማደሪያህ ለመምጣት የሚያቅዱ ፣ ጉዞ የጀመሩ ሰዋች "አንተን ብርታት ያደረጉ የላይኛውን መንገድ የሚያስቡ" ጥም ያለበት መንገድ ከእነርሱ የተነሳ ይለመልለማል፤ ይበረታሉ አይቀሩም።
ቁ 10 ደጁ መቆም፦ ደጅ የሚቆሙ defect ያላቸው ሰዋች ናቸው፤ እንደነርሱ መሆን ደግሞ ይመርጣል። ተገደው ደጅ ሚቆሙት እርሱ ይሻላል። ይሄ ሰው የእግ/ር ማደሪያ ይወዳል። ይሄ ሰው ከእግ/ር ቤት ጋር ያልተቆራየ ነገር የለውም ነፍሱ ስጋው ልቡ።
መፅሀፍ እንደሚነግረን የማደሪያ ለውጥ አድርጋል። ማደሪያው ያ ድንኳን ያ መቅደስ ነበር። ኃይለኛው የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሲመጣ የመቅደስ ሽግግር መጣ። በአለ አምሳን ለማክበር የመጡ አይሁዶች የመጡበትን በልሳን ቋንቋ በመስማታቸው በመደነቅ ወደ አዲሱ ቤተመቅደስ ተጨመሩ።
እግ/ር በቋሚነት የሕንፃ/የድንኳን ማደሪያነት አልመረጠም። በኀጢያት ምክንያት ከሰው ወደ ድንኳን /ሕንፃ ማደሪያ ለጊዜያዊነት ማደር ጀመረ። እግ/ር አሁን ኦሪጅናል ቤቱን አግኝቶአል፤ በክርስቶስ ደም ማደሪያ በመቀደሱ ፤ የእግ/ር ቤት ተሰራ ፤ በመንፈሱ አደረበት ፤ ይሄ ሕዝብ ወደ ዓለም ተበተነ። ‘የእግ/ር ሕንፃ፣ የእግ/ር ቤተመቅደስ፣ ለእግ/ር መኖሪያ ለመሆን ምትሰሩ ናቸው፣ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሰሩ፣ በእግ/ር ማደሪያ ቤት ’ እግ/ር አይታይም ግን ደግሞ ማደሪያው ሆንን። የእግ/ር ቤተመቅደስ እናንተ ናችሁ። ትልቅ ጥያቄ ላንሳ፦ ምን ያህል ማደሪያውን ትወዳላችሁ? እግ/ር ሕያው ማደሪያውን፣ ቤተክርሰቲያንን ፣ሰዋችን ምን ያህል ትወዳላችሁ? እዚህ ያሏችሁን ጊዜ ምን ያህል ትወዳላችሁ? በኮቪድ ሰዓት ይሄን ማደሪያ ምን ያህል ናፈቃችሁ። ጌታን የምትወዱትን የምትገልጡት ማደሪያውን በመውደድ ነው። ብዙ ሰው ሕብረት አያደርግን በሰብብ "ማደሪያዋችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው’ የሚሉ ጥቂቶች ናቸው። እግ/ር ከአንድ ድንጋይ ተፈልፍሎ የተሰራ ቤት የለውም፣ ብዙዋች ተገጣጥመው በሚሰሩ ድንጋዮች የሚሰራ ነው። በንፁህ ልብ ጌታን የሚጠሩ ሰዋች እኛሉ በመንቀፍ ብቻ ከማደሪያወቹ አንለይ ፣እርሱ አድሮበታል።