እውነተኛ እስራኤል (የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል 27)
Vložit
- čas přidán 20. 02. 2024
- ኢየሱስ ክርስቶስ በእውነተኛ እስራኤልነቱ የእስራኤልን የእግዚአብሔር ልጅነት ወክሏል። ከዚህም የተነሣ ለእስራኤል የተነገሩ ብዙ ትንቢቶች የተፈጸሙት በእርሱ ሕይወት ነው። የሐዋርያው ማቴዎስም ጥረት፣ የጌታ ኢየሱስ ሕይወት ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የሚጋጭ ሳይሆን፣ ለእስራኤል የተገቡት ተስፋዎች ሁሉ ፍጻሜ መሆኑን እስራኤላውያኑ ተደራስያን እንዲገነዘቡ ነው። ለእስራኤል የተሰጠው ተስፋና ኪዳን በኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተፈጸሙ እንጂ እንዳልተሻሩ የምናምነው ለዚህ ነው። እነዚህ ክፍሎች እንደሚያስተምሩን፣ “ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው” ማለት “ኢየሱስ እውነተኛ እስራኤል ነው” ማለት ነው። ጌታ ኢየሱስ በእስራኤል ቦታ ገብቶ እርሷ ማድረግ ያቃታትን ሁሉ ሊያደርግ የቻለ፣ እርሷ መሆን የተሳናትን ሊሆን የቻለ እውነተኛ እስራኤል (The True Israel)፣ በዚህም የእግዚአብሔር ልጅ ነው።
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይ ይህንን ትምህርት ሁሉም እንድሰማ የትውልድ ልብ ይከፈት ❤❤😢😢😊
Amen
እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ መንፈሳዊ አባታችን ጳውሎስ!!
አሜን
Thank you, Paulos! Blessings.
God bless
እናመሰግናለን 🙏🙏
Got bless
ወንድሜ ፖዬ , ስላንተ እግዚአብሔር ይመስገን የፀጋ ሁሉ ባለቤት እርሱ ነውና አሁንም ፀጋ ይብዛልህ ❤❤።
እግዚአብሔር ይስጥልኝ
ስለ ሴቶች አገልግሎት የተወሰነ ነገር ብትለን
ዐውዱ አይፈቅድም
ጶል ጌታ ይባርክህ ቁጥር ስታነብ ትንሽ ቀስበል
እሺ