በማዕበሉ ላይ ጌታ - ኢየሱስ (የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል 21)
Vložit
- čas přidán 25. 09. 2023
- በመዝሙር 107፥23-30 እንደ ተገለጸው ማዕበሉን ጸጥ ባሰኘው አምላከ እስራኤልና ጌታ ኢየሱስ ማዕበሉን ጸጥ በማሰኘቱ መካከል (ማር. 4፥35-41) የሚታየው ተመሳሳይነት እጅግ ትኵረት ይስባል። ያህዌ በባሕሩ ረብሻ ላይ ሥርዐት በማስፈን ሕዝቡን ከውሃ ማዕበል እንደሚታደግ ሁሉ፣ ኢየሱስም በደቀ መዛሙርቱ ሕይወት ተመሳሳይ ኀይሉን ገልጧል። እግዚአብሔር በመርከበኞቹ ላይ የገለጠውን፣ ኢየሱስም በገሊላ ባሕር በደቀ መዛሙርቱ ላይ አድርጓል። ብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ብቻ የሰጠው ይህ ኀይል የናዝሬቱ ኢየሱስም እንዴት ሊኖረው ይችላል? አሳማኙ ምላሽ፣ ኢየሱስ በሥጋ የተገለጠ የእስራኤል አምላክ መሆኑ ነው።
መልካም ትምህርት ነዉ ።ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይባርክህ ተባረክ
Amen
የምወድህ ወንድሜ ፖዬ ጌታ ረዥም እድሜ ና ጤና ይስጥህ ባንተ አገልግሎት ብዙ ተባርኬአለሁ ❤❤ ፀጋ ይብዛልህ ።❤❤❤
Amen
Egziabher yistiline, Paulos! Learning a lot as usual.
Amen my sister
1:49 መልካም ት/ም ነው ።ትልቅ የቃልመገለጥ ነው ።ከዚህም በላይ እ/ር አምላክ የቃል እውቀት ይሰጥህ
Amen
ጌታ ይባርክ እውነተኛ የክርስቶስ ወንጌል ነው በጌታ ኃይል በርታ እኔ ወ/ዊ ወልድየስ ጥብቡ ነኝ ከገጠር አሁን የድግር መጽሐፍ ቅዱስ ለመማር አድስ አበባ መካነ የሱስ ዶም ነኝ ለበለጠ የሕይወት ቃል ለመረዳት ነው ወንድም የሚከተለውን
Amen
God bless
ወንድሜ ጳውሎስ "የእግዚአብሔር ልጅ " የሚለው መፅሀፍህን ሳነብ አጠገቤ ሆነህ የምታስተምረኝ እስኪመስለኝ የምታነሳቸው ነጥቦችን እረዳቸዋለሁ ። ጌታን ስላንተም እኔንም ፀጋውን ስላበዛልኝ አመሰግነዋለሁ ።I strongly recommend you all to read his book.God bless you.
Blessings
እንዴት ነህ ወንድሜ ሰላምህ ይብዛ።
ኦዲዮቹን እስከዚህ ድረስ ያሉትን ያዳመጥኮቸው ከመጽፉ ጋር አብሬ እየተመለከትኩ ነው።
በጣም በሚገርም መልኩ አሳማኝ በሆነ መልኩ ኢየሱስ በምድር ላይ ፍጹም ስው ሆኖ ሳለ በአምላክነቱ ደግሞ ፍጹም አምላክ ሆኖ ከአምላክነቱ ለአንዲትም ሰከንድ ሳይጎል እንደተመላለሰ በጣም ገብቶኛል።
ጥያቄ 1ኛ ዮሐንስ 2፥6 ላይ የተመሰረተ ነው።
“በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።”
- 1ኛ ዮሐንስ 2፥6
በዘህ ጥቅስ እርሱ እንደ ተመላለሰ
እኛ እንድንመላለስ ያዘናል።
እርሱ በምድር ሲመላለስ ደግሞ መለኮትም ጭምር እንጂ ሰው ብቻ አልነበረም።
እኛ ግን ሰው ብቻ ነን እንጂ አምላክ አይደለንም ስለዚህ 1ኛ ዮሐንስ 2፥6 ትንሽ ገለጥ አድርገህ እንዴት በህይወታችን እንደሚተገበር አስረዳኝ።
ስላንተ ግን እግዚአብሔርን በጣም አመሰግናለሁ ብዙ ጥያቄ የሚሆኑብኝ ነገሮች አሳማኝ በሆነ መልኩ በዚህ መጽሀፍ ተመልሶልኛል።
ጌታ አንተንና ቤተሰብሀ አብዝቶ ይባረክ።