ቁርአን ለምን በአረብኛ ወረደ || Why the Quran Was Revealed in Arabic [David Wood Amharic]
Vložit
- čas přidán 19. 12. 2023
- I found this video useful, so I translated it to the best of my ability. Use this link to find the first video I translated from. I apologize for the minor mistakes I make.
• Why the Quran Was Reve...
What the Quran REALLY Says about the Gospel • ቁርአን ስለ ወንጌል ምን ይላል? ከ...
መልካም ዜና
የምስራች፣ የምስራች፣ የምስራች! የምስራች ማለት መልካም ዜና ማለት ነው። የእግዚአብሔር ቃል ደጋግሞ የሚነግረን ይሄ መልካም ዜና ምንድነው? ዛሬ፣ በእግዚአብሔር ረዳትነት፣ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለተጠቀሰው ስለዚህ መልካም ዜና እንነጋገራለን። ነገር ግን ስለ መልካሙ ዜና ከመነጋገራች በፊት ስለ መጥፎው ዜና ማስታወስ አለብን።
ምንድነው መጥፎው ዜና? በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ በኋላ አዳምንና ሔዋንን በምድራዊዋ ገነት ውስጥ እንዳስቀመጣቸው ታስታውሳላችሁ። እግዚአብሄር እንዲያውቁት፣ እንዲወዱት፣ እንዲታዘዙት እና ለዘላለም እንዲያከብሩት ፈጥሯቸዋል። ይሁን እንጂ እግዚአብሔር እነሱን ለመፈተን አዳምን እንዲህ አለው፡-
“በገነት ካለው ከዛፉ ፍሬ ብሉ፥ ነገር ግን እንዳትሞቱ በገነት መካከል ካለው ከዛፉ ፍሬ አትብሉ አትንኩትም።”
መጥፎው ዜና አዳምና ሔዋን እባቡን ማለትም ከተከለከለው ዛፍ ፍሬ እንዲበሉ የፈተናቸውን ዲያብሎስን ማዳመጣቸው ነው። የአዳምና የሔዋን ኃጢአት እነርሱንና ዘሮቻቸውን ሁሉ በመበከል በዓለም ላይ ችግርንና ሞትን አመጣ። ብዙ ጊዜ እንደምንሰማው፡ "ወረርሽኝ መነሻው ላይ ብቻ አይወሰንም!" የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጥፎ ዜና ይነግረናል፡-
“ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥...
እነሆ፥ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ፥ በኃጢአተኝነትም ስላደረጉት ስለ ኃጢአተኛ ሥራቸው ሁሉ ዓመፀኞችም ኃጢአተኞች በእርሱ ላይ ስለ ተናገሩ ስለ ጭከና ነገር ሁሉ ኃጢአተኞችን ሁሉ እንዲወቅስ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ።” (ዕብራውያን 9፥27 ይሁዳ 1፥15)
ስለዚህ፣ መጥፎው ዜና ሁላችንም ኃጢአተኞች ነን እናም የእግዚአብሔርን የጽድቅ ፍርድ መጋፈጥ አለብን! ይሁን እንጂ፣ መልካሙ ዜና (የምስራቹ) በዚያው በገነት ውስጥ፣ በምረቱ ባለጠጋ የሆነው እግዚአብሔር፣ አንድ ቀን ከድንግል የሚወለድን ኃጢአት የሌለበትን ሰው ወደ አለም እንደሚልክ ማስታወቁ ነው። ይህ ቅዱስ ሰው፣ ይህ ጻድቅ አዳኝ፣ ለአዳምና ለዘሮቹ ሁሉ ኃጢአት ለመክፈል ራሱን መስዋእት አድርጎ ይሞት ነበር። ለኛ የሚገባን የኃጢአት ቅጣት በዚህ ኃጢአት በሌለበት አዳኝ ላይ ይወድቃል። አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሠሩበት ቀን እግዚአብሔር የሰበከው ወንጌል (የምስራች) ይህ ነው። እግዚአብሔር የዚህን አዳኝ መምጣት ለማወጅ ብዙ ሰዎችን ተጠቅሟል፣ እንዲሁም መሲህ ይባላል። እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ አንድ ነገር አውጀዋል፣ ስለዚህም እርሱ ሲመጣ እግዚአብሔር የሾመው እርሱ መሆኑን ሁሉም ይገነዘባል። ለምሳሌ ያህል፣ ከመሲሑ መምጣት ሰባት መቶ ዓመታት ቀደም ብሎ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስ፣ መሲሑ እንዴት እንደሚወለድ ተንብዮአል። "ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።"( ማቴ. 1:23፤ ኢሳ. 7:14 ) ሚክያስ የተባለ ነቢይ ደግሞ መሲሁ ከሰማይ መጥቶ በቤተልሄም መንደር በምድር ላይ እንደሚወለድ ትንቢት ተናግሯል። በትክክል መሲሑ የተወለደበት ቦታ ይህ ነበር። ሆኖም ሚክያስ ይህን ትንቢት የተናገረው መሲሑ ከመወለዱ ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ነው። ነገር ግን ነቢያት የመሲሑን መወለድ ብቻ አላወጁም። በተጨማሪም መሲሁ በኃጢአተኞች ምትክ መከራ እንደሚደርስበትና እንደሚምት ትንቢት ተናግረዋል። ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ሰዎች መሲሑን እንደሚንቁት፣ እንደሚያሰቃዩት፣ እጁንና እግሩን እንደሚወጉ እና እንደሚገድሉት ጽፏል። ዳዊት የመሲሑን ሞት ማወጅ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር መሲሁን ከሞት እንደሚያስነሳውም ተንብዮአል፤ ይህም እግዚአብሔር የአዳምን ልጆች ከኃጢአት ቅጣት ለማዳን የላከው አንድና ብቸኛ አዳኝ መሆኑን አረጋግጣል።
ስለ መሲሁ መወለድ ብዙም ክርክር የለም፣ ነገር ግን ብዙዎች በሞቱና በትንሳኤው ይሰናከላሉ። ሰዎች የላከውን መሲህ ሲያዋርዱት እግዚአብሔር እንዴት ሊቆም እና ሊመለከት እንደሚችል አይገባቸውም። ብዙ ሰዎች ሊረዱት ያልቻሉት ነገር መሲሑ ለኃጢአታችን እንዲህ አይነት መከራ እንዲደርስበት ያቀደው እኛን የሚወደን አምላክ መሆኑን ነው። ነገር ግን ነቢያቱ እንዲህ ሲሉ አውጀዋል፡- “እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።”
- (ኢሳይያስ 53፥10)
ነቢያትን እናምናለን? አዎ እናምናቸዋለን እንላለን። ነቢያትን በእርግጥ የምናምን ከሆነ የጻፉትንም ማመን አለብን። ነብያት የራሳቸውን ሃሳብ እንዳልተናገሩ ማስታወስ አለብን። እግዚአብሔር የሚናገሩትን በመንፈሳቸው ውስጥ አኖረ። እንግዲያውስ እነዚያን ነቢያት ለማመን ብንቃወም፣ ማንን ነው ምንቃወመው? የምንቃወመው እግዚአብሔርን ነው። ምክንያቱም ነቢያት መሲሁ ኃጢአትን ለማስወገድ መስዋዕት ሆኖ እንደሚሞት ትንቢት እንዲተነብዩ ያነሳሳው እርሱ ነውና።
{የሚቀጥለው ማሊክ የሚባል ሰው የግል ምስክርነት ነው።} እዚህ ጋር ቆም ላድርገውና እንዴት በኢየሱስ ክርስቶስ አማኝ እንደሆንኩ ልንገራችሁ። በወጣትነቴ በቀን አምስት ጊዜ ለመጸለይ እና አመታዊ ጾምን ለመጾም ታማኝ ነበርኩ፣ ነገር ግን ከሞትኩ በኋላ ወዴት እንደምሄድ አላውቅም ነበር። ዙሪያዬ ያሉትን ሁሉ ጠየኩ፣ ሆኖም ግልጽ የሆነ መልስ አላገኘሁም። ወንጌልን (ኢንጂልን) ሳጠና ግን፣ ከሞቴ በኋላ ወዴት እንደምሄድ ማወቅ እንደምችል አወቅሁ፤ ምክንያቱም መሲሁ ኢየሱስ ራሱ በወንጌል እንዲህ ይላል፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” (ዮሐንስ 5፥24) እንዲሁም እንዲህ ብሏል፦ “ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤” (ዮሐንስ 11፥25) ስለዚ፣ ራሴን ለማዳን ከራሴ ጥረት ንስሃ ገብቼ ነቢያት ሁሉ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት ይቀበላል" ብለው ትንቢት በተናገሩለት መሲህ አመንኩኝ (ሐዋርያት 10፥43)። ተስፋዬን ሁሉ ወስጄ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ አስቀመጥኩት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ለመንፈሴ ሰላም አምጥቶላታል። አሁን ህሊናዬ አይረበሽም። ኢየሱስ በመስቀል ላይ ከሰራው ሥራ የተነሳ የወደፊት እጣዬ በሚያስደንቅ ሁኔታ ብሩህ ነው። በሕይወቴ እንደ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር፣ አንዳንድ ጊዜ ችግር እና መከራ ያጋጥመኛል ምክንያቱም እምነቴ ከዘመዶቼ እና ከጓደኞቼ አስተያየት ስለሚለያይ፤ ግን ሰላም አለኝ። የእግዚአብሔር ሰላም ልቤንና አእምሮዬን ሞልቶታል። ይህን የሰጠኝ ኢየሱስም እንዲህ ይላል፦ “ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ።” (ዮሐንስ 15፥18) “ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።” (ዮሐንስ 14፥27) እና ወዳጆች ሆይ፣ ጌታ ለእኔ እና በእኔ ያደረገውን ለእያንዳንዳችሁ ሊያደርግ ይችላል። ካንተ ወይም ካንቺ አንድ ነገር ይጠይቃል፡-ሙሉ ልብህን እንድትሰጠው። ሙሉ ልብሽን እንድትሰጪው። የቀረውን እሱ ያደርገዋል። ጌታ ኢየሱስ ራሱ እንዲህ ብሏልና። "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤" (ማቴ. 11:28-29)
እግዚአብሔር ታላቁን ማዳኑን መቼም ቢሆን አይሸጥልህም ወይም አይሸጥልሽም። እንዲሁ ያለ ምንም ዋጋ (ከእናንተ ባልሆነ ዋጋ) በነጻ ሊሰጣችሁ ነው ሚፈልገው። መልካም ስራ፣ ፀሎት (ሶላት) እና ፆም በውስጣችሁ ጥሩ ስሜት ይሰጡ ይሆናል፣ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ፅድቅ አያረኩም! ወደ እግዚአብሔር ገነት የምትገባበት/የምትገቢበት መንገድ አንድ ብቻ ነው።
1.) በመጀመሪያ ኃጢአተኛ እንደሆንክና አምላክን ለማስደሰት የሚያስችል ኃይል እንደሌለህ መገንዘብ ይኖርብሃል።
2.) ከዚያም ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ እንደሆነ፣ ኃጢአትህን ለማስወገድ እግዚአብሔር በመስቀል ላይ እንዲሞት እንደ ላከውና እግዚአብሔር የዘለአለም ሕይወትን ይሰጥህ ዘንድ እንዳስነሳው ማመን አለብህ።
የኦሮምኛውን ቻናሌን ለማግኘት ይህንን ተጫኑ👇
/ @dhugaanniboqachiisa
አስተያየታችሁን በውስጥ ማድረስ የምትፈልጉ ይህንን የቴሌግራም ሊንክ ተጠቀሙ👇
t.me/BibleAndMe
ኧረ Coment ላይ ቢያንስ እንደምትወዱኝ ንገሩኝ🙄 ሁሌ እንደምትወዱኝ ብትነግሩኝ አይከፋኝም😁🥰
እንወድሀለን
ወንድማችን በጣም እንወድሃለን እግዚአብሔር አምላክ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅህ❤
betam new yemwdh berta❤
በርታልን ግን ቴሌ ግራምክን እንዴት ነው የማገኘው ቪዲዮችክን ማውረድ እፈልጋለው🙏🙏
እወድሀለሁ ጀግና በርታ ወንድሜ!
በጣም እንዎድሃን ከእኛ በላይ ደግሞ እየሱስ በጣም ይዎድሃ ሰለምዎድህም እየሱስ ለራሱ አላማ የመረጠህ በእየሱስ ተሠርጠሃል ወንድመ ቀጥልበት❤❤❤❤❤
🥰🥰
gilt.machiberer.ametu.degimo.lezich.amem.bilachihu.gehaneb..betam.asamami.newu.ichin.fetena.inkuwan.mekuwa.kwam.ykitowachihu.mekemek.yemiti.gebut.lehitan.lij.kinkuwan..indih.ayinet.kumneger.tebilo.ayiworam.yihe.yemistirawiwu.mehaber.yemiyakenabirewu.zede.newu.shilimat.yagenibetal.yihen.yahil.sewu.kageneh.yihen.yahil.yikefelihal.yibalal.iwukwt.albasewochin.iyasebasebe.yiketachewal.benegerachin.layi.inesu..iwunet.iye.meselchewu.newu.imiketelut.fetari.irdachewu.mechereshawu..zemen.layi.achiberbari.yibezalina.tetenkeku.bilo..fetari.asawukonal.isa.aleyihi.salatu.wosalam.mim.tenagirotal.
❤❤❤❤❤❤❤ተባረክ ወንድሜ እየሱስ ይወድሃል እኔም እወድሃለሁ ፀጋ ብዝቶልሃል
በጣም እንወድሃለን በርታ ወንድማችን እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሁን❤
ገራሚ መረጃዋችን ስለምታደርሰን እናመሰግናለን።በርታ ወንድማችን።
ወንድሜ ጌታ ይባርክህ ስለ እስልምና ብዙ ነገር እንድናውቅና ለሙስሊሞች ወንጌልን መስበክ እንድንችል ድፍረትም እንድናገኝ የወንጌል በር ሆነሀል እንወድሃለን ❤❤
አመሰግናለው🙏🥰
ተባረክ እግዚአብሔር አገልግሎትህን ያስፋው
በጣም ነው እምንወድህ ወንድማችን ❤❤❤
ፀጋው ይደግፍ ወንድማችን❤❤❤❤❤
ጌታ ይባርክህ ዘመንህ ይባረክ እንወድሀለን
እንወድህለን ለዘላለም ተባረክ
ተባረክ ወንድማችን !ክርስቲያኖች ለሌሎች ተደራሽ እንዲሆን SHARE እናረግ እንዲሁም Like
ወድማችን የምትሰራው በማስረጃ ነውና የምታደርገውም መልካም ተግባር በመሆኑ እግዚአብሔር አምላክ ይባርክህ።
እናመሰግናለን
አምላኬ ሆይ ልቤን ወደ አንተ መልሰከ በቤትከ አኑርኝ ልቤን አጠከርው ከርሰትነዩን አለምልመው ተመሰገን 🙏
እንዳለ ውሸት ነው
ለምሳሌ ከውሸቶቹ መካከል እስቲ አንዱን ጥቀስና እንወያይበት። ከውሸቶቹ መካከል ከባድ የምትለውን ምረጥና።
ዋናዉ ነገር አላህ ያወረደዉ መሆኑን ማወቁ ጥሩ ነዉ ይህ ጉዳይ እስልምናን ለመረዳት ጥርጊያ መንገድ የሚከፍት ሲሆን
ቁርአንን ለመረዳት ‹ መጀመሪያ የሆሊዉድ ነጭ ፎቶ ከቤትህ ሰቅለህ ፈጣሪየ ከማለት የፀዳ አይምሮ ይኑርህ ›
እኔ ቤቴ የለኝም። ምክንያቱም፣ ልክ ስላልሆነ። አንተም እንደ መሐመድ በማታውቀው ነገር ሰውን ትከሳለህ አይደል!!! ትገርማላችሁኮ። አላህ ክርስቲያኖች የሚያመልኩት ሶስት አማልክትን ነው፣ እነሱም አላህ መርየም እና ኢሳ ናቸው ብሎ ቀባጠረ፣ አንተ ደሞ ስእል ታመልካላችሁ ብለህ ትከሰናለህ። ምናለ ወደ መጽሐፋችን ሄዳችሁ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ንላል ይሄ ደሞ ልክ አይደለም ብትሉን፣ ከፈጣሪያችሁ ጀምሮ በሆኑ ጥቂት ሰዎች የመንደር ላይ ወሬና ሰህትተት መመራል። እረ አላህንም ከመንደር ወሬ ውጣ በሉት እናንተም ውጡ።
እስኪ ስለቁርዓን ትክክለኛነት መደስኮርህን አቆየውና እስኪ እየሱስ እኔ ጌታ ነኝ አምልኩኝ ያለበትን አንድ አንቀጽ ንገረኝ
@mikigerji እስኪ አንዳንድ ጥያቄዎች ተመልሰው ይሆን ብላችሁ ቻናሉን ጎብኙ። የተመለሰ ጥያቄ ደግሞ መጠየቅ ሰነፍ ያስብላል። ለማንኛውም መልሱን ይህንን ሊንክ ስትነካ ታገኘዋለህ።👇
czcams.com/video/WSVwHk9DYAg/video.html
@@mikigerjiእየሱስ ለብቻው ጌታ ሊሆን አይችልም
@@mikigerji ye yohanis wangel 14:6
በጣም እናመሰግናለን❤
Wow ሁሌ ምወደው እናባረክበት ፕሮግራም ❤❤❤❤ ጌታ ይባርክህ ወድሀለው
እየሱስ ይባርክህ ምርጥ ነው ቀጥልበት❤
እግዚአብሔር ይባረክህ እንወድካለን
ዘመንህን የይባረክ እንወድሃለን ❤
ዋው በጣም እናመሰግናለን❤❤❤❤❤
በጣም ነው የምንወድህ bro በርታልን❤
ከኛ በላይ እግዚያብሔር ይወድሀል እመቤታችን ቅድስት ድግል ማርያም ታጠንክርህ በአንተ ብዙ የማላውቀውን አሳውቆኛልና ክብሩ ይስፋ ለመድሀኒያለም
በዉነት እግዚአብሔር ያሰነሳ ነህ ብዙ እሰልሞች ይድናሉ።
😅😅😅
ትልቅ ሰው ገራሚ ገራሚ ቪድዮ ነው የምትልቀው በጣም ጠቅሞኛል
🥰🥰🥰 አመሰግናለው።
Wow so much nice thank ❤️❤️🙏🏾🙏🏾🙏🏾🙏🏾
ተባረክ ብርክርክ በል
አሜን!🙏🥰
@@ewnetyasarfal እግዚአብሔር አምላክ ይመስገን አሜን ♥️🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ወንድሜ ተባረክ
ተባረክልን❤
LA ILAhA ILE Allah❤❤❤❤getaye
Kante wichi behaque
Migezut amlak yelem
Atwelldm atwelledm
Ke sw hidem alwetahim
Ya Allah❤❤❤❤❤❤
wushatamoch edime likachehun matalale bicha ur prophet is terrorist and also you
Bezi ewent be mimsel kal wesheten medebke ayechalem ewent hule ewent nw ewenet demo eysus nw eysus yeberalchu
user Allah ጣኦት ንቃ አምልጥጥጥጥጥጥ
😂😂😂😂 yanchii Allah shibaa new 🤣
እግዚአብሔር ማሰትዋልን ይሰጣቸው እውነተኛ መንገድ ይምራቹ
JESUS IS LORD JESUS IS LOVE ❤GLORY TO JESUS BLESS IN JESUS NAME
Thank you
በጣም እንወድሀለን በጣም❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤🙏
Awo betam new dess milew Egziabhir ybarkachu
ትልቅና ደማሚት የሆነ ስራ ነው ወንድሜ ገና ከሙስሊም በተአምራት የሚታጀቡ አገልጋዮች ይፈልሳሉ
ተባረክ 🥰🥰🥰
አላወክም እንጂ አእምሮ ያላቸውን ማስተዋል የሚችልቱን ክርስቲያን ወንድሞቻችንን ወደ ኢስላም እየጋበዝክል ስለሆነ በጣም እናመሰግናለን
እንኳን ደስ አለህ🥰
በእውነት እንደምወድህ በርታ ወንድሜ እግዚአብሔር አምላክ ከጎንህ ይሁን በርታ 🙏 ጆርጂዬን ጋና ድሮ ነው የምወደው ምከንያቱም ደግሞ ለዘክር ናይክ በምሰጣው መልስ ነው ❤
😂😂😂😂 በእዉነቱ ወንድሜ በጣም ጡሩ ትምርት ነዉ እናተ በዋሻችሁ ቁጥር በስልመናየ ላይ ያለኝ እምነት ይጠነክራል አልሀምዱሊላህ
የኔም ፍላጎት ወይ የለየለት ሙስሊም እንድትሆን ወይ ደሞ እንድትጥለው ማድረግ ነው። ስለዚ ተሳክቶልኛል ማለት ነው እግዚአብሔር ይመስገን። ምክንያቱም ሰው ላመነበት ነገር በአግባቡ መኖር አለበት ብዬ አምናለው። ምክንያቱም እኔም እግዚአብሔር ልቤን ባይለውጠው ኖሮ የከፋሁ የሰው ልጆች ጣላትና ነፍሰ ገዳይ የዲያቢሎስ ልጅ ነበርኩ። ሰው በምድር ላይ መኖሩ የማያስደስተኝ ክፉ። እንደውም እናንተ ሙስሊሞች ትሻላላችሁ በያንስ ለሙስሊሞች ትራራላችሁ (በሃይማኖት ምክንያት)። እኔ ግን ቤተሰቦቼ እንኳን እንዲኖሩ የማልፈልግ ክፉ ሰው ነበርኩ። እውነቱን ለመናገር ክፉ ከሆንክ አይቀር ሙስሊም ሆነህ ባትገደብ እመክርሃለው። ህይወት ይሻለኛል አምላክ ወዶ የፈጠረውን ክቡር ፍጥረት ለምን አጠፋለው ካልክ ደሞ ልክ እንደ እኔ ወደ ጌታ ኢየሱስ ና። እውነተኛ ሰላምና እረፍት ያለው እሱን አውቆ በማመን ውስጥ ነው። ሰዎችን ከልብህ መውደድና ለእነሱ እስከመሞት ልታፈቅር የምትችለው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስታምንና በእሱ የሚያምኑ ብቻ የሚያውቁትን መንፈስ ቅዱስን ስትቀበል ነው። ስለዚ መሃል አትሁን። ወይ የለየለት ፍቅርና ደስታ ሰላም ወዳለበት ወይ ደሞ ወደለየለት ነፍሰገዳይነት ወይም ጂሃድ (የሰው ነፍስ ማጥፋት) ግባ። ከሁለቱም ሳትሆን መሃል ላይ አትባክን። ማለት የፈለኩት ግልጽ ነው፣ ወይ በደንብ መሐመድን ምሰልና በነፍሰገዳይነትህ ምርጥ ሁን ወይ ደሞ እንደ ኢየሱስ በሌሎች ፋንታ እስከመሞት ምርጥ ሁን። እወድሃለው🥰🥰
qonjit yetugari now islimna dasi yemiyasegno isk nigarg. isk inawora ba coment wude isk laz tiyaqe malis malishlg wude mohamadn nabiya yadaragawu manow isu irasun barasu nabi nagn silachu indet taminalachu isk iz bet mamitatish kallarash nigargn mani now mohamad nabiy now yalew biyans isu nabiy indehona inditawoq misikr ayasifalgm malat now Ala mohamad yane barha now lane tazaji now bilowachu quran layi tsigiwal isu nabiy indehona miyasayi masiraja isk hamich tiyaqe sititayaqu isu nabiy indehona quran yinagaral tilalachu quranun uko irasu now yaworadwu so.inatee isu balachu mangad now lik inde iwur mithedut minm miskr yelam isu nabiy indehona yemiyasay
አንድ አብሮክ የተማረ አብሮክ ያደገ ሙስሊም ጓደኛ ይኖርካል እስኪ ለሱ ሙስሊም ሰው ገደሉ ይላል ወይ በልና ጠይቀው
@mikigerji እንኳን ይህንን ሊነግረኝ እንደ አብዛኞቻችሁ ቁርአን እንኳን በእጁ የለም። ቁርአን ራሱ የሰጠሁት እኔ ነኝ፣ እንዲያነበው። እንደ አብዛኞቻችሁ ግን በገገማው ይዳረቅ ነበረ።
እና እስልምና ሰው በመግደል ገነት እንደሚገባ ከነገረው ለምን ጠዋት ማታ በግንባሩ ይሰግዳል አንተን ግሎ ገነት መግባት እየቻለ???
ወንድም በዚሁ ቀጥልበት
Yemer bexam new mewdeh tebarek
ጌታ አብዝቶ ይባርክ ወንድሜ ተሎ ተሎ ልቀቅልን 🙏😊
🥰🥰
Tebarek berta tsega ybzali🙏🙏🙏
ጌታ እየሱስ ከአንተ ጋር ይሁን እንወድሀለን 👏❤
በርታ ወንድሜ
Egzhbher yibarkh wendme stega yibzalih
tebarek wendme ewedhalew
Thank you,for revealing the hidden secrets of the truth. God bless you.
ሙስሊም ኢትዮጵያዊስ አረቡ አላህ ጉድ ሰራቸው😢😢
በጣም ነዋ❤❤❤
Never give up bro!!!
❤❤❤❤❤እነወድሃለንተባረክ
wow Tebarekln❤❤❤❤❤❤
Tebarek wondmachn❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
❤ tebarek
Why was the Qur’an revealed in Arabic?
In the name of Allah, the Most Gracious, the Most Merciful
Answer
The first and the perhaps most obvious reason is already referred to in the Qur’an, namely that because the Messenger of Allah (peace be upon him) who was to announce this message was an Arab, it is only natural that the message be announced in his language:
وَلَوۡ جَعَلۡنَـٰهُ قُرۡءَانًا أَعۡجَمِيًّ۬ا لَّقَالُواْ لَوۡلَا فُصِّلَتۡ ءَايَـٰتُهُ ۥۤۖ ءَا۠عۡجَمِىٌّ۬ وَعَرَبِىٌّ۬ۗ قُلۡ هُوَ لِلَّذِينَ ءَامَنُواْ هُدً۬ى وَشِفَآءٌ۬ۖ وَٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ فِىٓ ءَاذَانِهِمۡ وَقۡرٌ۬ وَهُوَ عَلَيۡهِمۡ عَمًىۚ أُوْلَـٰٓٮِٕكَ يُنَادَوۡنَ مِن مَّكَانِۭ بَعِيدٍ۬
And if We had sent this as a Qur’an in a foreign language (other than Arabic), they would have said: “Why are not its Verses explained in detail (in our language)? What! (A Book) not in Arabic and (the Messenger) an Arab?” Say: “It is for those who believe, a guide and a healing. And as for those who disbelieve, there is heaviness (deafness) in their ears, and it (the Qur’an) is blindness for them. They are those who are called from a place far away (so they neither listen nor understand). [41:44]
Another important reason concerns the audience, which was to receive the message. The message had to be in a language understood by the audience to whom it was first addressed, i.e. the inhabitants of Makkah and the surrounding areas:
وَكَذَٲلِكَ أَوۡحَيۡنَآ إِلَيۡكَ قُرۡءَانًا عَرَبِيًّ۬ا لِّتُنذِرَ أُمَّ ٱلۡقُرَىٰ وَمَنۡ حَوۡلَهَا وَتُنذِرَ يَوۡمَ ٱلۡجَمۡعِ لَا رَيۡبَ فِيهِۚ فَرِيقٌ۬ فِى ٱلۡجَنَّةِ وَفَرِيقٌ۬ فِى ٱلسَّعِيرِ
And thus We have revealed unto you (O Muhammad SAW) a Qur’an in Arabic that you may warn the Mother of the Towns (Makkah) and all around it. and warn (them) of the Day of Assembling, of which there is no doubt, when a party will be in Paradise (those who believed in Allah and followed what Allah’s Messenger SAW brought them) and a party in the blazing Fire (Hell) [42:7]
The Qur’an contains revelation from Allah and the true nature of revelation is to guide mankind from darkness to light:
الٓرۚ ڪِتَـٰبٌ أَنزَلۡنَـٰهُ إِلَيۡكَ لِتُخۡرِجَ ٱلنَّاسَ مِنَ ٱلظُّلُمَـٰتِ إِلَى ٱلنُّورِ بِإِذۡنِ رَبِّهِمۡ إِلَىٰ صِرَٲطِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَمِيدِ (This is) a Book which We have revealed unto you (O Muhammad SAW) in order that you might lead mankind out of darkness (of disbelief and polytheism) into light (of belief in the Oneness of Allâh and Islâmic Monotheism) by their Lord’s Leave to the Path of the All-Mighty, the Owner of all Praise. [14:1]
The revelation came in the language of the Messenger and his people in order that it might be understood:
إِنَّا جَعَلۡنَـٰهُ قُرۡءَٲنًا عَرَبِيًّ۬ا لَّعَلَّڪُمۡ تَعۡقِلُونَ
Verily, we have made it a Qur’an in Arabic, that you may be able to understand (its meanings and its admonitions).
In the process of understanding a message two steps are essential:
To receive the message correctly and completely, in this case, to receive its words correctly and completely.
To ‘decode’ it, to grasp the meanings of the message received.
Only the combination of the two elements, i.e. reception and decoding leads to a proper understanding of the message.
It is not correct to assume that understanding the Qur’an in order to take guidance from it depends upon direct knowledge of the Arabic language since there are numerous Arabic speaking people who do not understand the message of the Qur’an. Rather the Qur’an tells us that right guidance comes only from Allah:
‘This is the Guidance of Allah with which He guides whomsoever He will of His slaves….’ [6:88]
However, to understand the language of the Qur’an is a pre-requisite to fully grasp its meanings.
Only Allah Knows Best
Much Blessed ውንድምነት እወድሃለው ❤❤❤❤
እንወድሀለን
If you want to know anything about islam , ask everything
❤❤❤❤❤❤❤❤ በኢየሱስ አወድሀለሁ ወንጌል ብርሀን ነው
ለኛ የተላኩት ነብዩ መሀመድ ሰ አ ወ ጥሩ አድርገው በማስተማር የህወታችነነ መንገድ አሳይተውናል ።ይልቁንስ መጻፍእን መርምርና ሳይረፍድብህ እራስህንና መሰሎችህን ከእሳት አድን የሚሻልህ እሱ ይመስለኛል ።ጥራት ይገባ የአለማቱ ጌታ እስልምናን ለሰጠን❤❤❤
አላህ ሂድያ ይስጣቸዉ
Alhamdulillah Ala’a ni’amatil Islam ☪️ ❤❤
😂😂😂😂😂😂😂
ሳህ ወላህ እኛ ሙስሊሞች የምናመልከዉ አንተንም እኔንም እናተንም እኛንም ሰማይና መሬትን ሁሉንም የፈጠረ ጌታችንን አምሳል የሌለዉ የማይታይ የማይሳል እየሱስ/ኢሳ/አለይሂ ሰላም ሁሉንም ነብያቶች የፈተራቸዉ ሊገዙት ነዉ መቼ አምላካችሁ ነኝ ተገዙኝ አላችሁና ገናኮ ይመጣል ሞትን ሁሉም ነፍስ ቀማሽ ስለሆነ እሱም ሞትን ስላልቀመሰ እዉነታዉን ያኔ ትሰማላችሁ አሁን ያልተመለሰ ግን ከከሳሪዎች ነዉ ሙስሊም ሆናችሁ እንደተፈጠራችሑኮ ታዉቃላችሁ በመጸሐፍ ቅዱስም አንድም ቦታ ላይ ኢሳ/እየሱስ/ አድም ቦታ ላይ እኔን አምልኩኝ ጌታችሁ ነኝ አላለም እንደዉም አላህ አንድ ነዉ እሱን እንጂ ሌላ እንዳትገዙ አምላኬም አምላካችሁም አንድ ነዉ የሚለዉን ነዉ የተናገረዉ እሱ አምላኩን አልካደማ አላህን ታዛዥ የአላህ መልክተኛ ነዉ እኛም እንወደዋለን
Atesastu amelak haymanote ayesxem ement enji bemjmeriya kurhan lay yalewen gud bedeb eweki or eweke adelem lemamen lemesmat yemzgenene neger alebet adelm yamelak kal limsel betkekel masb bemichel sew erasu yetsafi ayedelem le ene mels kemsxet or kemsadeb befit kurhanun bedeb betergum anbebut eyesus geta nw eysus yeberalachu
Taberik
david wood vs mohamed hijab
david wood vs osman
gebtachu eyut
Thanks!
ይገርማል የመፃፉን ባለቤት ጠይቁ ብሎ ሲመሰክር ቁርአኑ እርስ በእርሰ አይጋጭም ይኤ አዚም ካልሆነ ቁጭ ያለ እውነት ያሳያል እንዴት ነው ነገሩ
we love you...blessed!!!
Betam dink timihirt🌷🌹🌷
Bebezu tebarek enewedekalen btm geta kante ga nw bereta
በጥሩ ሁኔታ ነዉ የምትገልፀዉ እግዚአብሔር ይባርኬህ
ዋው ነው በጣም።ዕፁብድንቅ
በርታ መልካም እያደረክ ነዉ
Tabark enwdhaln
geta yibarkih tebarek
በርታ።።
100% ትክክል ነህ
ወንድሜ በጣም ነዉ የምወድህ
🥰🥰
Tebark❤❤
God bless you
Surah...yemilw yetignaw sura lay new?
እንወድሃለን ❤❤❤
አላህ ያጠመመው ማንም አያቀናውም አላህ ያቀናው ማንም አያጠመውም
ዶክተር ዛኪርን ሰርች ብታደርጎ እውነተኛ መልስን ታገኛላችሁ በየትኛውም ቋንቋ ቁርዐንን ማውረድ የሱ ስልጣን እና ጥበብ ነው አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራን አሚን
እየመራችሁኮ ነው። እናንተ ግን ታዛዦች አይደላችሁም። እኛ ቀጥተኛውን መንገድ አግኝተነዋል። ቀጥተኛውና ብቸኛው መንገድ ኢየሱስ ነው። ስለዚ መንገዱ እየተነገራችሁ አሳየን እያላችሁ አትጨቅጭቁት፣ ልባችሁንና ጆሯችሁን ቼክ አድርጉት።
@@ewnetyasarfal እንደዛህ ካልክ እየሱስም ቀጥተኛ መንገድ መሆን አይችልም ከእስራኤል ውጪ😂😂😂
አላ ያልመረጣቸውን ምን እንዲሆኑ ነው የፈጠረን አጣሞ የፈጠረንን እራሱ ነው አደል?? እስኪ ልጠይቅ እስልምና ልክ የሆነ እምነት ከሆነ ለምን አለ አስቀድሞ ቀደረብን???
@@ewnetyasarfal እየሱስ የተላከው ለናንተ አይደለም ለእስራኤል ህዝቦች ብቻ እንጂ ከሱም በፊት ብዙ ነብያቶች ተልከዋል ለአለም ህዝብ እና የነቢያቶች መደምደምያ ለኔም ለናንተም የተላኩት ነብይ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ ናቸው ከእሳት መዳን የሚፈልግ የሳቸውን መንገድ ይከተል የሁሉም ፍጥረት ባለቤት የሆነውን አላህን በብቸኝነቱ አምላክነትን ይቀበል ይህ ነው እስልምና ማለት
@@ewnetyasarfalአሏህ የፈጠረን እሱን ብቻ እንድነመልከው ነው።ይህን ሳናረግ ከቀረን ደግሞ የከፋ ቅጣት እንደምጠብቀን ነግሮነል። እናንተ ደግሞ እየሱስ ጌታ ነው፣ለኛብሎ ተሰቀለ ምነምን ትላለችሁ ፣የተገኘው አምልኩኝ የለችሁ? እናንተ እደምትሉት ይሁንና ተሰቀለ፣ተሰቀየ እናም ተገደለ እናም እዚህ ጋ የምየስዘን ራሱንም እንዳለደነ ነው እናም አንተን ልየድነክ የምችለው እንዴት ነው? እንደዚህ ተወዘግባችሁ ተወዘግቦባችሁ የምትኖሩ ሰዎች መለት እናንተ ናችሁ።ነገ ፀፀተኛ ፀፀቱ መይጠቅው ቀን ከመምጣቱ በፊት ብጤ እና አምሰያ የሌላውን አሏህን ብቻ ተገዙ።
እጅግ በጣም❤❤🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤የምወድህ🎉🎉
🥰🥰🥰🥰🥰
እግዚአብሄርማሥተዋሉንያሥጠንለሁሉምሠው❤❤❤❤❤❤
Waww enwedh alen ketlbet ❤️
ጀግና ወንድማችን በርታ❤❤❤❤❤
Enam
Bertu bertu ❤❤❤
I love you so much God bless you my brother 👍🌹🌹🌹🌹🌹🌹
Tebareklnnn❤❤❤❤
እዉነት
እናንተ እያወቃችሁ እየመሰላችሁ... አበቃላችሁ
1 ኢንግሊዘኛ ቃል ስንት ትርጉም አለው
ብዙ ትርጉም አለው
አረብኛ ደግሞ 1 ቃል በጣም ብዙ ትርጉም አለው
1 የአረብኛን ቃል ለመተርጎም ብዙ አማርኛ ቃል ያስፈልጋል
የማይተረጎም ቋንቋ የለም። አውድ የሚባል ነገር አለ። አንድ መጽሀፍ የሚተረጎመው በአንድ ቃል ላይ ተመስርቶ ሳይሆን፣ በአረፍተነገሩ ላይ ከዛም ባለፈ በምእራፉ ላይ ተመስርቶ ነው። ስለዚ አንድ ቃል ብዙ ትርጉም አለው የሚለው ላለመተርጎም ምክንያት አይሆንም።
tsega yibzalih
We love u🙏
We love u by Jesus's love❤
Tabaraki እንወዳለን
በጣም አናመሰግናለን መንፈስ ቅዱስ አብዝቶ ይባርክህ ብክርስቶስ ፍቅር አንወዳሃለን ወንድማችን
We love you bro
ቀላል እወድሀለሁ
betam enwedhalem