የስላሴ አካል ሶስት ወይስ አንድ? [ለጥያቄዎ መልስ] Apostle Zelalem Getachew
Vložit
- čas přidán 21. 08. 2024
- Short Videos of Apostle Zelalem Getachew
teaching ll Inspirational ll Motivational ll revelation ll trinity ll ስላሴ
....................................................................................................................
#Apostle_Zelalem_Getachew #ApostleZelalemGetachew #ሐዋርያ_ዘላለም_ጌታቸው
መንፈሳዊውን አለም በሥጋዊ ዕውቀት መግለጥ ሰለማንችል ስለሥላሴ ጉዳይ ትተን የተገለጠውን ክርስቶስን አጥብቀን እንያዝ ብቻው አምላክ ነውና
ኧረ መሸፈንህ ነው ኦ.ጂ ....የተገለጠውን ኢየሱስን ለመስበክ የላከውን አባት(አብ) ማወቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው የተገለጠውን ክርስቶስ ማን ገለጠው እንዴት መጣ ???? መቼም ወልድ አብ ነው ኮት ነው ቱታ ነው እንደማትለኝ እርግጠኛ ነኝ አይደል🙄🙄🙄🙄
what an amazing explanation in brief!
"ya silasen mistir ba imnatachin lik naw miniradaw!" thank you, Blessed.
እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ ይባርክህ በርታ
እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ! ሐዋርያ ዘላለም በአንተ ትምህርት በብዙ ተጠቅሜአለሁ!!!
ከረጅም ጊዜ በኋላ ነው የማይህ። የአባቶችን መሠረት እያስተማርክ በመሆኑ እና የነቢያትና የሐዋርያት መሠረት ደግሞ ቅዱስ ቃሉ ላይ ማብቃቱን በመናገርህ ደስ ብሎኛል።
እኔ እንደገባኝ አብርሃም ይስሓቅም ያዕቆብም ሙሴ ዳዊት ሃዋርያት ነብያት እና ጌታ የሱስ ክርስቶስም እግዚአብሔር ስላሴ ነው ብለው አላስተማሩም። ስለ አብ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ሲያስተምሩ እግዚአብሔርን ከአንድ በላይ ነው የሚል ትምህርት አላነበብኩም። ሁልጊዜም ስለ አንድ እግዚአብሔር መፅሃፍ ሲናገር ስለ እግዚአብሔር አብ ብቻ ነው። ይልቅ ከትእዛዛት ሁሉ ፊተኛ የሆነውን ትዛዝ በመተላለፍችሁ ደግሞም በማስተማራችሁ ተጠያቂ ናችሁ።
የማርቆስ ወንጌል 12
29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥
30 አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። የቀደመው ትእዛዝ ካልተቀየረ እንዴት አዲስ ትምህርት ፈጠራችሁ? ሌላው ጌታ የሱስ ክርስቶስ የማየታይ አምላክ ምሳሌ ከሆነ እንዴት ብሎ ነው እግዚአብሔር ሶስትም አንድም የሚሆነው? እግዚአብሔር አንድ ነው ሲባለ ድግሞ በመለኮት ነው ብለሃል መለኮት ማለት ምን ማለት ነው? መፅሃፍ እግዚአብሔር አንድ ነው ሲል በመልኮት ነው ይላል? ይህን ፍልስፍና ከየት አገኘህው? ምንም የማስተማር ልምድ እንዳለህ ባውቅም ከጌታ መማር መልካም ስልሆነ ከስር ያስቀመጥኩትን የጌታችንን የየሱስ ክርስቶስን ትምህርት አሰላስለው።
የዮሐንስ ወንጌል 8
51 እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።
52 አይሁድ፦ ጋኔን እንዳለብህ አሁን አወቅን። አብርሃም ስንኳ ሞተ ነቢያትም፤ አንተም፦ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አይቀምስም ትላለህ።
53 በእውኑ አንተ ከሞተው ከአባታችን ከአብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማንን ታደርጋለህ? አሉት።
54 ኢየሱስም መለሰ አለም፦ እኔ ራሴን ባከብር ክብሬ ከንቱ ነው፤ የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው፤
55 አላወቃችሁትምም፥ እኔ ግን አውቀዋለሁ። አላውቀውም ብል እንደ እናንተ ሐሰተኛ በሆንሁ፤ ዳሩ ግን አውቀዋለሁ ቃሉንም እጠብቃለሁ።
አስተውል የጌታ የየሱስ ክርስቶስ አባት አይሁድ አምላካችን ነው የሚሉት ያህዌን ነው። ያህዌ ደግሞ ለዘላለም አንድ ነው። በአዲስ ኪዳንም ቢሆን በብሉይም።
Geta yebarekehe Hawareyawe Zelaleme!!🙏🙏🙌🙌🙌
የረዳህ እግዚአብሔር ይባረክ ተባረክ
ተባረክልኝ የእግዚአብሔር ልጅ
APOSTEL
ትልቅ ትምህርት ነው።ተባረክ መምህር
የክርስቶስ ትምህርት ስላሴ የሚል ሳይሆን እኔ ማን እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ የሚል ነዉ ኢየሱስን አይሁዶች ማን ነህ ሲሉት የመለሰላቸዉ መልስ ይህ ነዉ የዮሐንስ ወንጌል 8:25 ስለዚህ ኢየሱስ ቃል ሆኖ የነበረዉ በስጋ የመጠዉ አምላክ ነዉ እንጂ ልጅ ብቻ አይደለም
ኢየሱስ ወልድ እንጂ አብ አይደለም። አንድም ማስረጃ የለህም የዲያብሎስ ልጅ ነህ እሺ😏
@@sushinaty5864 ተወው የሴባልዮስ ልጅ ነው የእግዚአብሔር ልጅ ጠላት .....መሠረት የሌለው ኩቱም ጃኬቱም እርጥብ ስጋ ምናምን ከየት ከየት እንደሚያመጡት የማይታወቅ ጉድ እኮ ነው የሚያስተምሩት የተፃፈውን የሚክድ ከእንጨት የደረቀ ጨለምተኝነት ነው ያለባቸው እነዚህ ሰዎች ዳግም ካልተወለዱ በቀረ የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርሱም መቼም አብ ወልድ አይሆንም ወልድም አብ አይሆንም እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ እንደዚህ ብሎ የሚያስተምር መፅሀፍ ቅዱስ የለንም ። ዘልዬ እግዚአብሔር ይባርክህ በጥሩ ሁኔታ አስቀምጠኸዋል።
Tbarek❤❤❤❤❤❤❤❤❤ zlalem
You are blessed
Tbarek❤❤❤❤❤❤❤❤❤ zelalm
Tabarek silasen mawok ina nanan ye hiwot guday naw
God blessed you Apostle
You are blessed apostle.
Clearly three personality one idea.
Thanks beloved much blessings.♥
Good teaching
Thank you so much yene Tyaki neber
Blessed man Apostle 🙏
ተባረክ
Stay blessed memihir.
Blessed apostle
you are blessed.
Tebark
tebarek
Stay blessed
ከኋላ ወደ ፊት መግለጽ ወይም መተንተን ለምን አስፈለገ? ስማቸው በተቀመጠበት ሥርዓት ብተነተን ይሻላል እላለሁ። አመሰግናለሁ
አባቴ በመሆንህ ኩራት ይሰማኛል
ግን እኔ ብቻዬን ነኝ ብሎ ሶስትነት አለበት ማለት አይከብድም ለምንስ እስራኤል ስላሴን አይቀበልም መዳን ከአይሁድ ነው ስላለ ቃሉ ይህ የመፅሀፍ ቅዱስ ቃል አይደለም
Slasen banawkew addis ftret kemehon ykeleklenal
አብ በወልድ ውስጥ ሆኖ አብ በመንፈስ ቅዱስ ሆኖ ይገለጣል ማለት ነው? እግዚአብሔር በወልድና በመንፈስ ቅዱስነት ይገለጣል እንጂ እሱ አንድ ነው ማለት ነው?
Kmesafkudusi,Kelle,lemin,yastemiralu
ፊደላቱ የለም እንጂ ትምህርቱ እንዳለ ግልጽ ነው። ማስተማር ያስፈለገው ደግሞ በሂደት ቤተክርስቲያን ለገጠማት ቀጣፊ የሀሰት ትምህርቶች መልስ እንዲሆን ነው
ወንድሜ በምድር ላይ ያሉት የተደበላለቁ ቋንቋዎች መንፈሳዊውን አለም እንዳነረዳ የተደበላለቀ ሐሳብ አምጥቶብናል
Bzu temrebetalehu amesegnalehu gn tyake neberegn MENFES KIDUS amlak nw
የስላሴ ትምህርት አስ
የማይታይ አምላክ አብ ነው? አንተም ብለሃል። እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየም ይላልና
ኢየሱስ ክርስቶስ ታይቶአልና
እንደት ነው? ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው የምትሉት? እግዚአብሔር ሁሉት ልሆን ይችላል?
ተመልከቱ
ጥያቄው አብና ወልድ የሉም ሳይሆን አብና ወልድ የአንድ አካል ባህሪ ወይስ የሁለት አካል ባህሪ የሚል ነው?
ሁለት አካላት ናቸው። አንዱ አባት ነው። ሌላው የአባቱ ልጅ ነው። አንዱ ልጁን ልኮልናል። ሌላው አባቱን በመታዘዝ ወርዶልናል። አንዱ ተጠምቋል። ሌላው ከሰማይ ድምጽ ልኳል። አንዱ በስጋው ወደ ሥላሴ አቅርቦናል። ሌላው በልጁ ወደ ሥላሴ ስቦናል። አንዱ ከሙታን ተለይቶ ከብሯል። አንዱ አክብሮታል። ከስም ሁሉ በላይ ስም ሰጥቶታል። ወልድ ይህን ማዕረግ ተቀብሏል። የሥላሴ አስተምህሮ የአዲስ ኪዳን ደም ስር ነው።
Eysuis,resul,abinew
ኢየሱስ አብን እንደ ሌላ የራሱ አካል ያለው አባት እንጂ እኔ አብ ነኝ አላለም። ይልቅ ወደ አብ በየዕለቱ ይጸልይ ነበር። ያለህበት ድርጅት ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስን በጤነኛ አእምሮ ብታነበው ኢየሱስ አብ ነው የምትልበትን ድፍረት አታገኝም ወንድሜ
ስላም ላንተ ይሁን ዘሌ እኔ ክርስቲያን የኦርቶዶክስ ህይማኖት ተከታይ ነኝ ትምህቶችህን እከታተላለው ስለ መጽሀፍ ቅዱስ ያለኝ መረዳት እና እውቀት እንዲሰፋ እና እንዲያድግ ትምህርተህ እረድቶኛል ዛሬ 1 ጥያቄ አለኝ በነዚህ የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ ያለህን መረዳት እንድታካፍለኝ ነው (እኔ ሰው በእምነት እንጂ በስራ እንደማይጸድቅ አምናለሁ ይህንም ብዙ የመጽሀ ቅዱስ ክፍል ያስረዳል ሮሜ 3፣28/ ገላቲያ 2፡16/ 3፡11/ ኤፌሶን 2፡8 ስራ የሚጠቅመው ለ አክሊል እንደሆነ አምናለው ጢሞ 2፡5/ 4/8) ነገር ግን በሌላ ክፍል ደግሞ እምነት ያለስራ የሞተ እንደሆነ ያስረዳል ያእቆብ 2፡14/17 ) ስለዚህ እነዚህ 2 ክፍሎች ላይ ስፋ ያለ ትምህርት ብትሰጠኝ ማለትም እንዲሁ ክፍሎቹን ስመለከታቸው የሚቃረኑ ይመስላል ሌላው ደግሞ የስራ እና የእምነት ህግን ብታብራራልኝ ደስ ይለኛል ሮሜ 3፡27።
ሰላም ጠያቂይ ዳዊት ይን ጭት ስለለው በቴሌግራም ወይም በዩቲብ ዳዊት ፋሲል ሚንስቴር በሚል ሊክ ግባ
ይኸዉልክ ወንድሜ በደንብ ስርአተ ነጥቦቹን እይ ያእቆብ መልእክት 2 ከ17 ጀምሮ በያእቆብ እና በሆነ ሰዉዬ መካከል dialogue ነዉ።
ኢየሱስ ልጅ ብቻ ነዉ ወይስ አብም ነዉ ?
ኢየሱስ ከዘላለምም ለዘላለምም ልጅ ነው: ልጅነት ባህሪው ነው። ከማረጉ በፊት ወደ አባቴና ወደ አባታቹ እሄዳለሁ ሲል አሁንም አባቱ ጋር እንዳለ ያስረዳናል። 🙏
Dear Br Do know a bout the teachings of trinty or you do not accept it at all?There are three personalities in the God head .
በነገራችሁ ላይ እግዚአብሄርን ሶስት የማድረግ ጥረት እግዚአብሄር ቀድሞ ያውቅ ነበር ምክንያቱን የእየሱስ ክርስቶስ መምጣት ይሄንን ውዥንብር እንደሚያስነሳ ስለሚያውቅ ሙሴን በታቦቱ ላይ የመጀመሪያ ትዕዛስ ዘዳግም 6፡4 እስራኤል ሆይ ስማ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው ብሎ እንዲጽፍ ያደረገው።አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሄር የተገለጠበት መንገድ ነው።አብ በራሱ ስጋ ተገለጠ እሱም እየሱስ ነው እየሱስ የአብ የሚታየው በሀሪው ነው መንፈስ ቅዱስ በሁሉ የሆነ የእግዚአብሄር መንፈስ ነው።እየሱስ በስጋው ወልድ ነው በመለኮቱ ግን አብ ነው ይሄ እኛ የምንቀንሰው የምንጨምረው ነገር አይደለም ቃል ስጋ ሆነ።እግዚአብሄር አንድ ነው።
Apostle ኢየሱስ ተመልሶ ሲመጣ የት ይኖራል ብለህ ታስባለህ?? እባክህ በዚህ ጉዳይ አንድ ቪዲዮ ብትሰራልን::
please read Judah 4. Jesus Christ is the only and lonely true God. so, there is no trinity in the bible.
No he is not lonely 😂
ወደ አባቴ ብሎ ነው የሄደው ወንድሜ ወደ አባትነት መልኬ አላለም
መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ ነው ማለት ወደ ውስጥ የሚገባ ማለት አይደለም። ቃሉ ግዕዝ ነው በግዕዝ ሰራፂ ማለት በተቃራኒው የሚወጣ ማለት ነው። ይህም ከአብ ና ከወልድ የሚወጣ ማለት ነው።
አንተ ጋኒን የሆንክ ሰዉየ
አንድ እግዚአብሔር መታመኛዬ ነው ከሚል ሰው እንደዚህ አይነት ቃል አይጠበቅም።
አንተ የአባትህ የዲያቢሎስ ልጅ !
ስድብ ከእግዚአብሔር አለመሆንህን ይገልጣል ተመለስ
አባቴ በመሆንህ ኩራት ይሰማኛል