ቃሉን በቃሌ ፰ | iRecite 8

Sdílet
Vložit
  • čas přidán 10. 01. 2024
  • አንተን እንዳልበድል፣ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
    መዝ 119፡11
    የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።
    ኢያሱ 1፡8
    ይህ እግዚአብሔር ለኢያሱ የሠጠው ትዕዛዝ ዛሬ ለምንኖር ለእኛ ለሁላችንም በረከት ያለው ትዕዛዝ መሆኑን አስተውለነዋል?
    መጽሐፍ ቅዱስን በቃል የመያዝ እና መልሶ የማለት ፕሮግራም
    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
    አጠናን
    በመጀመሪያ ሁለት ወይም ሦስት ጥቅስ መሸምደድ
    በቀን 10 - 15 ደቂቃ --በየቀኑ አንድ ወይም ሁለት ቁጥሮችን በድንብ መያዝ፣
    ከራሳችን ጋር ማዋሀድ
    ድምጽ እያሰሙ መደጋገም
    አንድ የጥናት ጓደኛ
    የራስን ድምጽ በመቅዳት ማዳመጥ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ድምጽ ቅጂዎች ማዳመጥ
    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
    በዚህ መጽሐፍ ቅዱስን በቃል የመያዝ እና መልሶ የማለት ፕሮግራም ሁላችሁም እንድትቀላቀሉን እንጋብዛችኋለን።

Komentáře •