+ ገድለ አባ በግዑ + ሰምታችሁ በረከትን አግኙ
Vložit
- čas přidán 31. 05. 2021
- የቅዱሳን ታሪክ / Yekidusan Tarik የፌስቡክ ገፅ
- / %e1%8b%a8%e1%89%85%e1%...
+++አባ በግዑ+++
አባ በግዑ፡- አባ በግዑ በመጀመሪያ ሽፍታ የነበረ ሲሆን በመንገድ ላይ ንብረት የያዘን ሰው ማንንም የማያሳልፍ ቀማኛ ሰው ነበር፡፡ ከኃይለኛነቱ የተነሳ ሕዝቡም ሁሉ ይፈራው ነበር፡፡ በእጁ ሰይፍና ጦር ይዞ ሊዘርፍ ወደ ወደደው ሀገር ይገባል፡፡ እየዘረፈ በሚያገኘው ገንዘብም ራሱን በተለያዩ ምግቦችና መጠጦች ያስደስት ነበር፡፡ ባማሩ ልብሶችም ይዋብ ነበር፡፡ ገንዘቡ የተወሰደበት ሰውም እርሱ እንደወሰደበት ባወቀ ጊዜ ዳግመኛ መጥቶ የተረፈውን ቀምቶ እንዳይወስድበት ምንም አይከሰውም ነበር፡፡ በጉልምስናው ኃይለኛና ብርቱ ስለነበር ወደ እርሱ ማንም አይቀርብ ነበር፡፡
በእንደዚህ ያለ የውንብድና ሥጋ ብዙ ዓመታት ከኖረ በኋላ አባ በግዑ በስም ክርስቲያን ነበረና ከዕለታት በአንደኛው ቀን መንፈስ አነሳስቶት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደ፡፡ ካህኑም ባየው ጊዜ ከመንገድ ገለል አደረገውና ‹‹የሕይወት ዘመንህን ሁሉ በከንቱ አሳለፍክ ዛሬ ስማ ልንገርህ፣ በዘመንህ ፍጻሜ እግዚአብሔር ይጎበኝሃል፣ በመንፈስ ቅዱስም ያድርብሃል፣ ፍጹም መነኩሴ ትሆናለህ፣ በብዙ መከራና ተጋድሎ ትኖራለህ በዚያም የነፍስህ መዳኛ ይሆናል፣ እግዚአብሔርንም ደስ ታሰኘዋለህ›› አለው፡፡ ከዚህም የበዛውን ብዙ ነገር ነገረው፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቁርባን ተቀበለ፡፡ ወደቤቱም ከተመለሰ በኋላ ካህኑ የነገሩትን እያሰበ ‹‹እስከመቼ በስንፍናዬ እኖራለሁ? እስከመቼስ የነፍሴን መዳኛ ሳላስብ እኖራለሁ? …›› እያለ አሰበ፡፡ ከዚህም በኋላ ከዘመዶቹ ተለይቶ ከሀገሩ ወጥቶ ሄደና ወደ ባሕር ዳርቻ ደርሶ የቅዱስ እስጢፋኖስን ቤተ ክርስቲያን እጅ ነሣ፡፡ ከመነኮሳትም ማኅበር ገብቶ እነርሱን ማገልገል ጀመረ፡፡ አባ በግዑ በእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ልቡ ተመልሶ ከመነነ በኋላ ግን እስከሞተበት ዕለት ድረስ የላመ እህል ሳይቀምስ ኖረ፡፡ ምግቡን የዛፍ ፍሬና ሜዳ ላይ የሚበቅል ቅጠል አደረገ፡፡ ዓቢይ ጾም ሲመጣም ከሰኞ እስከ ቀዳሚት ሰንበት ምንም ሳይቀምስ የሚጾም ሆነ፡፡ ውኃንም ሳይጠጣ ኖረ፣ ማንም ሰው ሳያውቅብ ለ5 ወር ምንም ውኃ ሳይጠጣ ተቀመጠ፡፡
ከ5 ወር በኋላም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደ አባ በግዑ መጣና ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ሰላም ለአንተ ይሁን! በምን ትታወካለህ? ምንስ ያሳዝንሃል? ››አለው፡፡ አባ በግዑም ‹‹ጌታዬ ከውኃ ጥም የተነሣ በጣም ስለተጨነቅሁ ነው›› አለው፡፡ መልአኩም ነጥቆ ወደ ገነት ወሰደውና ከገነት ቅጠል አንሥቶ አቀመሰው፡፡ ወዲያም የአባ በግዑ ሰውነት ታደሰች፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ውኃ ሳልጠጣ ተጋድሎዬን እፈጽም ይሆን!›› የሚለው የኅሊና መታወክ ከእርሱ ጠፋለት፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አባ በግዑ ለሚወደው ለአንድ ወዳጁ ለማንም እንዳይናገር በእግዚአብሔር ስም ካስማለው በኋላ ለ5 ወር ምንም ውኃ እንዳልጠጣ ምሥጢሩን ነገረው፡፡ ያ ወዳጁም ይህን ሲሰማ ደንግጦ አለቀሰ፡፡ አባ በግዑም አብሮት አለቀሰ፡፡ ወዳጁም ‹‹እስከዛሬ ከውኃ የተከለከለ በማን ዘንድ ሰማህ? አሁንም ቅዱሳን መነኮሳትና አበ ምኔቱ አያምኑህም፡፡ ይህን ምሥጢር ዛሬ ብሸሽግ በመጨረሻ ይገለጣል፡፡ ሕዝቡ፣ ነገሥታቱና መኳንንቱም ይህን ነገር ይሰማሉ ነገር ግን አያምኑም፡፡ አሁንም የምነግርህን ስማኝና ትኅርምቱን ትተህ ውኃ ጠጣ›› አለው፡፡ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑም ‹‹የነገርከኝ ሁሉ እውነት ነው ሐሰት የለውም ነገር ግን እኔ ከዚህ በኋላ እስክሞት ድረስ ዳግመኛ ውኃ እንዳልጠጣ ስለ እግዚአብሔር ትቻለሁ፡፡ ሰዎች ባያምኑ እኔ ምን ገዶኝ፣ ነገር ግን በዚህ ገድል እግዚአብሔር ረዳት ይሆነኝ ዘንድ ጸልይልኝ›› አለው፡፡
ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ብረት አመጣና ሰንሰለቶችን ይሠራለት ዘንድ ለአንጥረኛ ሰጥቶ አሠራ፡፡ ያንን ወዳጁን ጠራውና እጆቹንና እግሮቹን በብረት ችንካር እንዲያስረው አዘዘው፡፡ ‹‹አበ ምኔቱን ጥራልኝ›› አለውና ጠራለት፡፡ አባ በግዑም አበ ምኔቱ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ሲመጣ በፊቱ ሰገደለትና ‹‹አባቴ ሆይ! የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እፈጽም ዘንደ በላዬ ላይ ጸልይልኝ›› አለው፡፡ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ከበዓቴ አልወጣም፣ ሰውም ወደኔ አይገባም›› አለው፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐም በላዩ ከጸለየለት በኋላ ‹‹ለእኔም ጸልይልኝ›› አለው፡፡ አባ በግዑም በቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን በአባ ኢየሱስ ሞዐ እጅ ቁርባንን ከተቀበለ በኋላ እጆቹንና እግሮቹን በብረት ችንካር ታስሮ ብቻውን ዘግቶ በጽኑ የተጋድሎ ሕይወት ኖረ፡፡ በዓቱንም ዙሪያውን መውጫ መግቢያ እንዳይኖረው መረገው፡፡ ለምግብ የሚሆነውን የዛፍ ፍሬና የሜዳ ቅጠል ማስገቢያ የሚሆን ትንሽ ቀዳዳን አበጃና ያ ወዳጁ ያስገባለታል፡፡ አባ በግዑም ያንን በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ይመገባል፡፡
የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ በእንዲህ ዓይነት ጽኑ በሆነ የተጋድሎ ሕይወት ሲኖር ሰውነቱ ላይ ከቆዳውና ከአጥንቱ በቀር የሚታይ ነገር እስኪጠፋ ድረስ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ፡፡ ውኃንም እስከ ሰባት ዓመት ድረስ አልጠጣም፡፡ መቆምም አይችልም ነበርና መነኮሳቶቹ ለቁርባን በቃሬዛ አድርገው ወደ ቤተ ክርስቲያን ይወስዱት ነበር፡፡ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ በእንደዚህ ዓይነቱ ለመስማት በሚከብድ እጅ የበዛ ጽኑ ተጋድሎ ካደረገ ከብዙ ድካም በኋላ በዚህች ዕለት ታህሳስ 27 ቀን ዐረፈ፡፡ ጌታችንም ተገልጦ ታላቅ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ የአባ በግዑ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
ወዳጆች ሆይ! ይህንን ማን ያምናል!? ለሰው ምንም ውኃ ሳይጠጣ ሰባት ዓመት መኖር ይቻለዋልን!? ‹‹በብዙ ሲጋደሉ እንደኖሩ የቅዱሳንን ገድላቸውን ሰምተናል፡፡ ነቢይ ዕዝራ የዱር ዛፍ ፍሬ እየተመገበ ውኃም እየጠጣ በምድረ በዳ እየጾመ ኖረ፡፡ ነቢይ ኢሳይያስም የሜዳ ጎመን እየቆረጠ ከእርሱም እየተመገበ ውኃም እየጠጣ በተራራ እየጾመ ኖረ፡፡ እግዚአብሔር ስሙን ‹የበረሃ ኮከብ› ብሎ የጠራው የመነኰሳት በኩር የሆነ አባ እንጦንስና አባ መቃርስም በደረቅ ኅብስትና በውኃ ብቻ ሲጋደሉ ኖሩ፡፡ እኚህ ምድራዊያን ሲሆኑ ሰማያውያን ሆኑ፡፡ ነቢይ ኤልያስም በኅብስትና በውኃ ብቻ በምድረ በዳ ሲጋደል ኖረ፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ግን ሰባት ዓመት ሙሉ ውኃ ሳይቀምስ ኖረ፡፡ ከመነነ በኋላ እስከሞተበት ዕለት ድረስ እህል የሚባል አልቀመሰም፡፡ እርሱ ግን ራሱን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ ያደርግና በትህትናም ሆኖ ስለ ኃጢአቱ ሁልጊዜ ያለቅስ ነበር፡፡
ይህም የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ይህን ሁሉ የተጋደለ በራሱ ኃይል አይደለም፤ በእግዚአብሔር ኃይል ነው እንጂ፡፡ አንተም ወንድሜ ሆይ ራስህን ዕወቅ፡፡ ምንም ተጋድሎን ብታደርግ ጾምኩ፣ ተራብኩ፣ ስለ እግዚአብሔርም ብዬ ራሴን አደከምኩ፣ እግዚአብሔርንም ስላገለገልኩ በሥራዬም እድናለሁ አትበል፡፡ መጨረሻህን አታውቅም፡፡ አንተ ግን ስለ እግዚአብሔር ብለህ ራስህን ኃጥእ አድርግ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ያጸድቅሃልና፡፡ ወዳጄ ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ እንድትመሰገን ራስህን አታመስግን፤ ሌሎችም ያመሰግኑህ ዘንድ አትውደድ፡፡ ክብር ታገኝ ዘንድ ትሕትናን ገንዘብ አድርግ፡፡›› (ገድለ አባ በግዑ)
ያባታችን ያባ በግዑ ርድኤት በርከታቸው ፀሎታቸው ይደርብን አሜን
አሜን አሜን አሜን የአባታችን የቅዱስ አባ በግዑ በረከት ይደረብን❤ በዚች ምድር ቸሩ ፈጣሪየን እደኔ ያሳዘነ የለም። አቤቱ የአባቶቸ አምላክ ማረኝ💔💔💔😢
አሜን አሜን አሜን ቃለ ሂወትን ያሠማልን❤ የአባ በግዑ በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ፫
Amen amen amen kel hiwet yasemalin ❤❤❤
አሜን አሜን አሜን በረከታችሁ ይደረብኝ
Amen Amen Amen kale hewt ysmalna 💙🙏💙🙏💙🙏
አሜን አሜን አሜን ቃለ በረከት ያሰማልን የቅዱስ አባ በግዕ በረከት ቃል ኪዳን ይጠብቅን ይሄን እደሰማ የፈቀደ አምላካችን ስሙ የከበረ የተመሰገነ ይሁን
አባ በግዕ ነምላክና ነጊርካ ብጰሎትካ ሓግዘና።ካብ ጰላኢ ድያብሎስ አድሕነና አሜን።ምስ አምላከይ አራክበኒ፡ፈጣርየይ ካብ ኩሉ ችግራት አድሕነኒ፡ ባርከኒ በእንተ አባ በጊዕ መሓረኒ ፡በእንተ አባ በጊዕ መሓረኒ፡በ እንተ አባ በጊዕ ባርከኒ አሜን። ኦ እየሱስ ክርስቶስ መሐረኒ አሜን
አሜን አሜን አሜን ቃለህይወት ያሰማልን የአባታችን የአባ በግዑ በረኬታቸው ይደርብን አሜን
አሜን አሜን አሜን የአባታችን በረኬት ረደኤት ቃልኪዳናቸው በኛላይ ይደረብን
አሜን አሜን አሜን በረከቱም ይሕደረና አባ በግዑ
አሜን፫ግዜ በረከታቸው ረድኤታቸው አድሮብኝ ከተያዝኩበት አኔን ክንፈሚካኤል እና ወለተሃናን ለምስክርነት ያብቃን ያድርገን።አሜን፫ግዜ ።
አሜን አሜን አሜን
ቃለ ህይወትን ያሰማልን🙏🙏🙏♥♥♥
የአባ በግዑ በረከታቸው ረደየታቸው ይደርብን።አሜንአሜንአሜን። ሰይፈ ሚካኤል በፀሎቶ ምህረትን ቸርነትን እንደደረግልኝ ፀሎትና በረከቶ አይለየኝ።አሜን አሜን አሜን።
አሜን አሜን አሜን የአባታችን በርከት ረድኤታቸው ቃልኪዳናቸው ይደርብን
አሜን አሜን አሜን በረከታችው ይደሪብን ቃል ህይወት ያስማልን
አሜን አሜን አሜን ቃል ህወት ይስመዐልና 🙏🙏🙏💒💒💒
አሜን አሜን አሜን ቃል ሂወት ያሰማልን በርከታችሁ ይድረብን
የቅዱሳን በረከት ይደርብን ቃለ ህይወት ያሰማልን
አሜን የአባ በግዑ በረከታቸዉ ይደርብን አባቶቸ ወ/ፃዲቅ እያላችሁ አስቡኝ እባካችሁ በስደት ላይ ነኝ ችግር ዉስጥ ነኝ እየጨነቀኝ ነዉ አስቡኝ
አሜን አሜን አሜን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን መምህራችን
አሜን አሜን አሜን ቃል ህይወት ያሰማልን
የአባታችን በረከታቸው ይደርብን ስለ እሳቸው ብሎ ይማረን ይቅር ይበለ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቤቱ እንደ እኛ በደል እና ሀጢያት ሳይሆን እንዳተ ቸርነት ማረን ይቅር በለን የወለተ ማርያምን ነፍስ ስለሳቸው ብለህ ማርልኝ😢😢😢
የአባታችን የአባ በግዑ ቃልኪዳናቸው አይለየን ይባርከን ቃለሂወት ያሰማልን የሰማነውን በልባችን ያኑርልን አሜን!
አሜን አሜን አሜን እንካን አብሮ አደረሰን
ቃለሂወትን ያሰማልን❤❤❤❤❤
ቃለህይወት ያሠማልን የአባታችን አባ በግዑ ረዴኤት በረከት ይደርብን አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመስገን በእለተ እረፍታቸው ገድለቸውን እደሠማ የፈቀ አምላክ የድንግል ማርያም ልጅ እግዚአብሔር ይመስገን👏👏💞💞💞💞👏👏👏💒💒👏👏
አሜን አሜን አሜን
ቃለ ህይወት ያሠማልን በድሜ በፀጋ ያቆይልን
የአባታችን የአባ በግዑ ሃብተ ረዴኤት ከኛጋር ይሁን አሜን///
አሜን አሜን አሜን ቃለ ህይወት ያሰማልን አባታችን የቅዱሳን ፃለት ልመና ምልጃ አይለየን በርከታችህ ይድርብን
አሜን አሜን አብታችን በረከታቸው ይደርብን የሰማነውን በልባችን ያሳድርብን ለመምህርም ቃለ ህይወት ያሰማልን ያገልግሎት ዘመንህንም ይባርክልን
አሜን ቃለህወት ያሠማልን ወንድማችን❤❤❤
Amen amen amen berktachew yideriben
Amen Amen Amen KAL hiwot yasemalen bendeme betena yitebekilen abatachin berketo yiderben yekidusu Abatachin berketachiw yiderben beberketachiw yasebun 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Amen Amen Amen 🙏.
ቃለ ሒወት የሰማልን ለኛም ላደመጥነም ረደኤት በረከታቼው ይደርብን አሜን
አቤቱ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ስነ እነዚህ መስተጋድል ቅዱሳን ቃልኪዳን ስትል ማረኝ ከክርስትያን ወገን የሚያስቆጥር አንዳች ምግባር የለኝምና።
Amen Amen Amen bereketachw yedrbn❤❤❤❤
Amen ye abatachen berektacha yedreben
አሜን አሜን አሜን እግዚአብሔር ይመሰገን
አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏
እግዚአብሔር ይመሰገን አሜን አሜን አሜን
በረከት ረድኤት ናይ ኣቦና ይሕደረና
Amen brketu ydrsen egzhbher yetbkiln
አሜን አሜን አሜን❤❤❤❤
አባበፆሎቱአስቡኝፍቅርቱአማኑኤል
ቃለሕይወት ያሰማልን።
የአባታችንን በረከታቸውን ያሳድርብን💠
ቃለህይወትን ያሰማል በእድሜ በጤና ያቆይልን
ቢሰሙት የማይጠገብ አገራችንን በፀሎት ማሩልን
ቃለ ሂወትን ያሰማልን የአባታችን የአባ በግዑ ረድኤት በረከቱ ይደርብን አሜን አሜን አሜን
አሜን 🙏😔
የቅድሱንን መጋደል በስመማ ው ቁጥር እኔ ምንም መግባርና ስራ እንደሌለኝ አውቃለሁ የአባቶቼ ቅድሳን አምላክ ይማረኝ ይቅር ይበለኝ
Amen 🙏
አሜን አሜን አሜንአሜን
Ye abatachen bereket yedereben..........amennnn.....
Amen Amen Amen kale hiwet yasemaln bereket ina tselot yabatachin aba begio kehulachin ga yhun ina latatachin degmo idme ina tsegha Egziabiher yabzalachew bewinet dess yemil sbket ina nbab 🙏♥️🙏
ኣሜንኣሜንኣሜን
kale hiwot yasemalin...memhr,ke bereketachew yasatfen.amen.
ቃለ ህይወት ያሰማልን
በረከታቸው ይድርብን
እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን አሜን አሜን ቃለ ህይወት ያሰማልን
አባታችን በረከቶ ይደርብን አሜን
ኣሜን ኣሜን ኣሜን ቃለ ህይወት ያሰማልን ፀሎት በረከታቸው የኣባ በግኡ ይደርብን 🙏🙏🙏
አባቴ በረከቶ ይደርብኝ
አሜን አሜን አሜን በእውነት የቅዱሳን በረከት እረደኤታቸው ይደርብን ቃለ ህይወትን ያሰማልን መምህራችን
Amen Amen Amen kalhewet yasemalin yabatachn bereketachew Amalajnetachew eredtachew yderbn egnanm lensha yabekan zend kidus fkadu yhunlin yenatun kidste kidusan dngl maryamn hager ethiopian tebkln enenm tebkegn kekifu neger Amen yderegln 💙💛❤🥰🥰🥰🥰🥰🙏🙏🙏🙏🙏🙏💙💛❤🥰🥰🥰🥰🥰🥰💙💛❤🙏🙏🙏🙏🙏
🌹💐🌹💐🌹
አሜን አሜን ቃለ ህይወት ያሰማልን መምህራችን አሜን የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን ከቃል ኪዳናቸውም ያሳትፈን ቸር አምላክ
Amennnn ye Abatachen bereketachew yedereben 🤲❤ kale hiweten yasemalen 🙏 ye agelegelot zemenachehu yetebarek yehun 🤲
❤❤
እሜን🙏🙏🙏🙏
እየሱስ ይሰበክ
Abat hoi bereketu ederebin amen amen amen
አምላክ ለአባ በግዑ ቃል ኪዳን እንደገባለት ገድልህ የሰማህ እሳት አያያትም።እስከ 7ትውልብ እምርሃለሁ። እንደተባለ ፍቃድህ ይሁን ገድሉ እንድንሰማ ሃይልና መንፈስ ቅዱስ ስጠን።
አሜን አሜን አሜን።(3)
Kale hiwotin yasemalin
አሜን አሜን አሜን የአባቶቻችን እረዴት በረከታቸው ፀሎት ምልጃቸው አይለየን ቃለ ህይወት ያሰማልን መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን 🙏❤❤❤❤❤
🤲🤲🤲🤲
❤❤❤❤
አሜን አሜን አሜን በርከታቸው ቃል ኪዳናቸው ይደርብን😢
አሜን አሜን አሜን በረከተወ ይደርብን💒💐
💚💛❤
እውነት ነው😭😭😭😭😭😭💔💔💔
እግዚአብሔር ይመስገን
አሜን (3) ቃለ ሂወት ያሰማልን ክቡር መምህራችን
የጻዲቁ አባታችን ቅዱስ አባ በግኡ ፀሎት በረከታቸው ይደርብነ
አሜን ፫ግዜ ለኔ ለኃጥያተኛውና በደለኛው በረከታቸው አድሮብኝ ከተያዝኩት በሽታ እንድነሳ ይሁንልኝ ይደረግልኝ ።አሜን፫ግዜ ።
ኣሜን ኣሜን ኣሜን ብረክታችው ይደርብን👏👏👏
አሜን አሜን አሜን የባታችን በርከት አይለየንአሜን ፫//
Amaen amaen amaen
ኣሜን ኣሜን ኣሜን
ቃለ ሂወት የስማዓልና
አባት ሆይ በረከት ይደርብን
አሜን አሜን
አሜን
ያባታችን በረከታቸው ይደርብን
በእንተ በግዕ መሓረን ክርስቶስ አሜን(3)
ኣሜን ኣሜን ኣሜን በረከታቸው ይደርብን
ቃል ሂወት ያሰማልን
Gedl New weys gedal
አባታችን ይቅርታ አድርጉልኝ አበቶችም ድያቆናትም ገድሉን ስያነቡ ለራሣቸው ያኔባሉ ማለቴ ሰያነቡ ድምፅ አውጥቶ ክርስትያኖች አንድሴሙ አያነብ ስያነብም የማንቤብ ችሎታ የሌለ ድያቆን ያነባል መለቴ እዬፌራ ስሌምያነቡ የክርስትያንን ጆሮ አይስብም ና ይህ ነገር እንድሻሻል እነፌልጋለን የማንቤብ ችሎታ የለሌ ድያቆንም ሆኔ ቄስ አያነብ መጀመርያ የማንቤብ ችሎታቼው ያዳብሩ ምመናንን በቻ አትወቅሱ መጄመርያ ብቃት ከናቴ ይጄመር
Selam
Amen Amen Amen kalehiwet yasemalin memhir
መዝሙሮቹን ፃፉልን እባካችሁን
አሜንአሜንአሜንበረከትህይደርብንአባቴሆይ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
እብድ ውሻ ግማታም
አሜን አሜን አሜን
እግዚአብሔር ይመስገን
በፀሎት ያስቡኝ አባቴ አልጋ ከያዝኩኝ አመታት ተቆጠሩ ክንፈሚካኤል ነኝ።
ንሠሐ ገብቼ ለመቁረብ እንኳንም አልቻልኩም ሳልቆርብ ሆስፒታል ገብቼ ኦፕራሲዮን ተደርጌ ወጣው ኢትዮጵያ ላሉት ለወንድሜ ንሠሐ አባትዐብነግራቸው ልጄልጄ ዶክሮቹ ላይ አድሮው በእለተ ቀኑ24ይዘህ የገባኻቸውፀበልናዕምነት በተክልዬ አማካኝነት ቆርብሐል ተጠንቀቅ አሉኝ።
እመብርሀን ታስበን😢@@legessetsegaye7390
አሜን አሜን አሜን