የኢትዮጵያ ይፋ በዓላት

Sdílet
Vložit
  • čas přidán 10. 06. 2024
  • ኢትዮጵያ በዓመት ውስጥ አራት “ብሔራዊ” ተብለው የተጠሩና ስምንት ሃይማኖታዊ በዓላትን እንድታከብር የሚደነግግ ህግ ፓርላማው ዛሬ፤ ማክሰኞ አፅድቋል።
    መስከረም አንድ የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ)፣ የካቲት 23 የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ሚያዚያ 23 የዓለም የሠራተኞች (የላብአደሮች) ቀንና ሚያዚያ 27 የዐርበኞች (የድል) ቀን በዓላት ናቸው።
    የሰማዕታት ቀን የካቲት 12፣ እንዲሁም የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ኅዳር 29 ታስበው እንዲውሉ ተደንግጓል።
    መስቀል፣ ገና ወይም የልደት በዓል፣ ጥምቀት፣ ስቅለት፣ ትንሣኤ (ፋሲካ)፣ ኢድ-አል አድሃ (አረፋ)፣ መውሊድ እና ኢድ-አል ፈጥር ስምንቱ በመላ ሃገሪቱ ተከብረው የሚውሉ የሃይማኖት በዓላት ናቸው።
    ታስበው እንዲውሉ ከተወሰኑት በስተቀር በ“ብሔራዊ” እና በሃይማኖታዊ በዓላት ቀናት፣ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ እንደሚሆኑ በዐዋጁ ተነግሯል።
    የደርግ መንግሥት ከወደቀ አንስቶ ያለ አዋጅ ሲከበር የቆየው "ግንቦት ሃያ" በዛሬው ድንጋጌ ውስጥ አልተካተተም።
    ከግማሽ ምዕት ዓመት በኋላ የወጣው አዲስ ዐዋጅ መደናገርን ያስወግዳል ብለው እንደሚያስቡ የህገ መንግሥትና ሕገ መንግሥት ጉዳዮች መምህርና ተመራማሪ አሮን ደጎል ለቪኦኤ ገልፀዋል።
    - - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -
    🔷 የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሊንኮችን በመጫን ይከተሉን።
    ፌስቡክ - / voaamharic
    ኢንስታግራም - / voaamharic
    X - / voaamharic
    ዌብሳይት - amharic.voanews.com
    የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ፡- / voaamharic
    ☎️የስልክ መሥመራችን 202-205-9942 የውስጥ መሥመር 14 ነው።
    📡 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።
    VOA Amharic reaches our audience on digital, radio, and TV, delivering news and content about Ethiopia, Eritrea, Africa, and the United States. We will also be bringing you Health Shows, Youth Shows, Democracy Field, Women’s Shows, and Sports Shows on different days, stay tuned.

Komentáře •