አላህ ይጠብቅህ ኡስታዝ እኛም በሰማነው የምንጠቀም ያድርገን
ሠላሙዋአሌኩምወራህመቱላሂወበረካቱ ኡስታዝ ሰዳት አቡመሪይም ትክክል ወላሂ ጀዛከላከይር
جزاك الله خيرا
እዉነት
Allah yetebeqek ustaz asakegn
ሽረ ሽረ ላይክ እያረጋችሁ ለብዙ ሰው ይድረስ ይሁን ባረክ አላህ ፊኩም
👍🌷
አላህ ይጠብቀን
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍
ክክክክክክክክ አላህ ይጠብቀን
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍
ሙሢሊምይትናቸህህህ
As wr wb Ustaz
_ Allah edmehen yarzemaw
_,kufu aynkah endehum emaylk ewkat Allah yesteh.
- hule Becker emtesabasebu yargachu
neuerer sew Kalb elegant Allah yedregaw.eganem besemanew emnsara Allah yadregan
_ be Allah zend tewedag besew Zensur tewadag Allah yargeh.Allauma Aminnn
ws wr wb
🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲😭😭😭😭
ሺኩረን
የዑለማዎች የአንድነትና የጋራ መግባቢያ ሰነድ!!
ክፍል -5
🍃🍃🍃🍃
አንቀጽ ሃያ አንድ
💠💠💠💠💠
ሙስሊሙ ህብረተሰብ እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በሀገሩ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ጉዳዮች ውስጥ ጉልህ ተሳትፎና አስተዋፅኦ ያደርግ ዘንድ እናበረታታለን፤ ይህን ተሳትፎና
አስተዋፅኦሊያጎለብቱየሚችሉኃይማኖታዊትምህርቶችንናፈተዋዎችንም እንሰጣለን፤በአንጻሩ ሸሪዓውን ያልጠበቁ፣ ሁለንተናዊ ተሳትፎዎችን የሚገድቡና ያልታረቁ አስተሳሰቦችን በሰከነ መንፈስና ጥበብ እናርማለን፡፡
አንቀጽ ሃያ ሁለት
💠💠💠💠💠
የሀገራችንን የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ እስላማዊ ቅርሶች፣እንዲሁም በረዥሙ የእስልምና ታሪካችን ያዳበርናቸውን ኃይማኖታዊ እሴቶቻችንን ሸሪዓው በሚፈቅደው አግባብ እንጠብቃለን፣ እናጎለብታለን፡፡
አንቀጽ ሃያ ሶስት
💠💠💠💠💠
በዚህ ስምምነት የተካተቱ ኃላፊነቶቻችንን በትጋት እና በቅን ልቦና መወጣት ግዴታችን መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም ሆነ ለወደፊት በየደረጃው ለሚሰየሙ የፌዴራልና የክልሎች የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የሙሉ ሰዓት አገልጋዮችና ኢስላምን በማስተማር
ላይ ያሉ የሀገሪቱ ዓሊሞች ሙሉ ጊዜያቸውን ለህዝበ ሙስሊሙ አገልግሎት ያውሉ ዘንድ ተገቢ የኑሮና የገቢ ሁኔታ ያለ አንዳች መድሎና ልዩነት እንዲመቻችላቸው አቅም የፈቀደውን ሁሉ መፈጸም የሁሉም ወገን ሀላፊነት መሆኑን ተስማምተናል፡፡
አንቀጽ ሃያ አራት
💠💠💠💠💠
ሙስሊሙ ሕብረተሰብ ሙስሊም ካልሆኑ ወገኖች ጋር የሚኖረዉ ግንኙነት መሠረታዊ ባህሪ የአብሮነት (ተሳሙህ)፣የመከባበርና የትብብር መንፈስን የተላበሰ ሰላማዊ ግንኙነት መሆኑን እናፀናለን፡፡ በመሆኑም ይህ የአብሮነት እሴት ተጠብቆ እንዲቆይ አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት ለማድረግ፣እንዲሁም ተገቢውን ትምህርትና መንፈሳዊ አመራር ለመስጠት ቃል እንገባለን፡፡ ለሀገራችን ሠላምና ልማት፣ እንዲሁም ለሕዝቦቿ አንድነት ጠንክረን እንሠራለን፤ሀገራዊ አንድነትን፣ወንድማማችነትን፣ብርቱ የዜግነት ስሜትንና አብሮነትን በፅናት እንደግፋለን፡፡ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ከሚኖሩ ወገኖች ጋር የእውቀትና የመልካም ልምድ ልውውጥ እንዲኖር በትጋት እንሰራለን፡፡
አንቀጽ ሃያ አምስት
💠💠💠💠💠
ከላይ የተዘረዘሩትን የስምምነት ነጥቦች በመጣስ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን፣ ስብስቦችንና ድርጅቶችን እንዲሁም የተሳሳቱ አመለካከቶች ሰለባ የሆኑ የሙስሊሙ ሕብረተሰብ አካላትን ከማግለል በመቆጠብ ተግተን እንመክራለን፤ አስፈላጊውን ትምህርት በመስጠትም ወደ ብዙሀኑ ህዝበ ሙስሊም እንዲቀላቀሉ መጣር ተቀዳሚ ሥራችን መሆኑን ተቀብለናል፡፡ በዚሁ ምክር ካልተመለሱ ቀደም ብሎ በአንቀጽ 12 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በኡለማ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው ተገቢው የሸሪዓ ስርዓት በተጠበቀበት አስፈላጊውን ብይን ማግኘት እንደሚገባቸው ተስማምተናል፡፡
አንቀጽ ሃያ ስድስት
💠💠💠💠💠
በሸሪዓችን ግምት ውስጥ ሊገቡ (ቦታ ሊሰጣቸው) በሚችሉ ጉዳዮች የተፈጠሩ የሀሳብ ልዩነቶች (ኺላፍ ሙዕተበር፤ አል ኢኽቲላፍ አል መሽሩዕ) ለሙስሊሙ አንድነት እንቅፋት ሊሆኑ እንደማይገባ በመስማማት፤ በተለይ ባለፉት 30 ዓመታት ገንቢ እውቀታዊ ውይይትና የሰከነ መደማመጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሳይፈጠር በመቆየቱና አካታች መሪ ድርጅት ባለመዋቀሩ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለከፍተኛ ኪሳራ ያጋለጠ መሆኑን በማመን ሊያሰባስበን፣ አመለካከታችንን ወደ ዋነኛና ገዥ መንገዶች ሊመራ የሚችል የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤትና የኡለማዎች ምክር ቤት ለማቋቋም ተስማምተናል፡፡
አንቀጽ ሃያ ሰባት
💠💠💠💠💠
ባሳለፍነው ታሪክ ለተመዘገቡት ጠንካራ ጎኖች እውቅና እንሰጣለን፤ የተሳሳትናቸውን ደግሞ እናርማለን፡፡ ላጠፋነው ሁሉ በቅድሚያ ከአላህ (ሱ.ወ.) ምህረት እየጠቅን እርስ በርስም ይቅርታ (አውፍ) በመባባል ወደ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ለመሸጋገር ተስማምተናል፡፡
አንቀጽ ሃያ ስምንት
💠💠💠💠💠
ይህ የስምምነት ሰነድ በተለይ በየደረጃው ለሚዋቀሩ የእስልምና ጉዳይ ምክርቤቶችና የዑለማ ምክር ቤቶች፣ ለመስጊዶችና ለመድረሳዎች የአሰራር ሥርዓት መሰረትና መነሻ እንዲሁም የበላይ ደንብ መሆን እንዳለበት ተስማምተናል፡፡
አንቀጽ ሃያ ዘጠኝ
💠💠💠💠💠
በዚህ ሰነድ የተካተቱትየኢትዮጵያ የእስልምና ኃይማኖት ሊቃውንት/ዓሊሞቸ ስምምነቶች በተሟላ መልኩ ተፈጻሚ እንዲሆኑ ህዝበ ሙስሊሙ፣ በተለይም ዳዒዎች፣ በገጠርም በከተማም ያሉ የዲኑ አስተማሪዎች፣ በየደረጃው ያሉ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶችና ሌሎች አግባብነት ያላቸው የእምነቱ ተቋማትየየበኩላቸውን የኃላፊነት ድርሻ እንዲወጡ በዚህ ታሪካዊ የስምምነት ሰነድ በሙሉ ድምጽአደራችንን እናስተላልፋለን፡፡
አንቀጽ ሰላሳ
💠💠💠💠
የዚህ ስምምነት መሰረታዊ (ኦሪጅናል) ሰነድ ማለትም የመጨረሻው ሕጋዊ አውቅና ያለው ሰነድ የሀገሪቱ የፌደራል የስራ ቋንቋ ቅጂ ነው፡፡ ሰነዱ በአረብኛና የክልል መንግስታት የሥራ ቋንቋዎች ይተረጓማል፡፡ የቃላት፣ የሀረግ፣ የአረፍተ ነገሮችና አንቀጾች ፍችና የሀሳብ ይዘት ወይም አንደምታ ለመረዳትም በዓሊሞች ውይይት ወቅት የተመዘገቡ ቃለ ጉባኤዎች መነሻ ይሆናሉ፡፡
አንቀጽ ሰላሳ አንድ
💠💠💠💠
ይህ የአንድነትና የትብብር መግባቢያና መመሪያ ሰነድ እንዳስፈላጊነቱ ወደፊት በሚቋቋመው የኢትዮጵያ ኡለማ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ አባላት በሙሉ ድምጽ ወይም በ 4/5 አብላጫ ድምጽ የቀረበውን ማሻሻያ ሲያጸድቁትና ይህም በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ በ 4/5 ድምጽ ሲጸድቅ ሊሻሻል ይችላል፡፡
ተፈፀመ
ጀዛኩሙላህ ኸይር ። ዉድ የሀገሬ ልጆች ኑ ወደ ቤቴ ፕሮፋይሌን በመጫን ሰበስክራይብ አርጉኝ ሀዲስን ቁርኣን እንማማር ጀዛኩሙሏህ ኸይር
ሰቄ
አዲሱ ቻላኔል ብተሰብ ይሁኑ
czcams.com/video/10PnV6ViE94/video.html